1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ፀረ ሕገ ወጡ የአልማዝ ንግድ ስብሰባ

ረቡዕ፣ ኅዳር 11 2006

ውዝግብ ከሚታይባቸው አካባቢዎች በሚወጣ የአልማዝ ማዕድን ንግድ አንፃር የተጀመረውን ትግል የማጠናከር ዓላማ የያዘው በእንግሊዝኛ ምሕፃሩ « ኬ ፒ ሲ ኤስ » በመባል የሚታወቀው « የኪምበርሊ ፕሮሰስ ሰርቲፊኬሽን ስኪም »

https://p.dw.com/p/1ALQq
GettyImages 149464644 TO GO WITH AFP STORY by Justine Gerardy A picture taken on July 6, 2012 shows an illegal miner displaying diamonds digged out of a disused mine in Komaggas. Three months ago 10 illegal miners died in an avalanche, while looking for gems on a disused mine. Illegal miners in South Africa are ready to risk death to chase a share of the mineral riches that shaped the continent's biggest economy. In sparsely populated Namaqualand, where the famed gem deposits run along the icy Atlantic Ocean to the Namibian border, diamond giant De Beers was once the top employer, but its mines were halted in 2008. The slowdown has emptied out the private mining towns, but has lured growing numbers of diggers from the area's other small settlements into the abandoned fields. AFP PHOTO / ALEXANDER JOE (Photo credit should read ALEXANDER JOE/AFP/GettyImages)
ምስል Alexander Joe/AFP/GettyImages

ቡድን ትናንት በደቡብ አፍሪቃ ጆሀንስበርግ ከተማ የአራት ቀናት ስብሰባ ጀመረ። ከ 81 ሀገራት የተውጣጡ ልዑካን ቡድኑ በሕገ ወጡ የአልማዝ ንግድ በተሰማሩ እና በሚገዙት አንፃር ጠንካራ ርምጃ መውሰድ በሚያስችለው የተሀድሶ ሀሳብ ላይ ይመክራሉ።
እአአ በ2003 ዓም የተቋቋመው « የኪምበርሊ ፕሮሰስ ሰርቲፊኬሽን ስኪም » ቡድን ፣ በምህፃሩ « ኬ ፒ ሲ ኤስ » ውዝግብ ከሚታይባቸው አካባቢዎች በሚወጣ የአልማዝ ማዕድን የሚደረገውን ንግድ ለማስቆም ጠንሮ ይታገላል። ይሁን እንጂ፣ ቡድኑ ከተመሠረተ ዛሬ ከአሥር ዓመታት በኋላም የአልማዙ ንግድ በአፍሪቃ የሚካሄዱ ውዝግቦች በቀጠሉበት ሂደት ላይ ሰፊ ድጋፍ እያበረከተ ይገኛል።
በስብሰባው መክፈቻ ላይ የተሰናባቿ የ« ኬ ፒ ሲ ኤስ » ሊቀ መንበር የደቡብ አፍሪቃ አምባሳደር ወሊሌ ንህላፖ ባሰሙት ንግግር፣ ተሳታፊዎቹ ልዑካን የቡድኑን ድክመት ለይተው በማወቅ ትግሉ የሚጠናከርበትን ዘዴ እንደሚጠቁሙ ተስፋቸውን ገልጸዋል።
« ቡድኑ ውዝግብ ከሚካሄድባቸው አካባቢዎች የተመረተን አልማዝ በሚመዘግብበት ስራው፣ ከድህረ ውዝግብ በኋላ በነዚህ አካባቢዎች በሚነቃቃው የመልሶ ግንባታ እና የልማት ተግባርም ላይ ርዳታ ሊያቀርብ ይችላል። ለቡድኑ ትልቁ ፈተና የሚሆነው በሕገ ወጡ ንግድ አንፃር የጀመረውን ትግል ማጠናከር እና የሕዝቦችን ኑሮ ማሻሻል መቻሉ ነው። »
በብራስልስ የሚገኘው ለማዕድን ኩባንያዎች የሚሟገተው የአንትዎርፕ የዓለም የአልማዝ ማዕከል ፕሬዚደንት አቪ ፓዝ « ኬ ፒ ሲ ኤስ » ራሱን ሕገ ወጡን የአልማዝ ንግድ ለመታገል ለሚቀርቡ አዳዲስ ተሀድሶ ሀሳቦች ክፍት ማድረጉን አሞግሰዋል።
የዓለም የአልማዝ ማዕከል በ« ኬ ፒ ሲ ኤስ » ውስጥ የተነቃቃውን ተሀድሶ፣ እንዲሁም፣ አልማዙ በሚወጣባቸው እና በቀጥታ የርስበርስ ጦርነት በማይካሄድባቸው አካባቢዎች በሚኖሩት ማህበረሰቦች ላይ በሚፈፀመው የኃይል ተግባር አንፃር ትግሉን ማስፋፋቱን ጭምር ይደግፋል። »
ይሁን እንጂ፣ የሲቭሊ ማህበረሰብ ጥምረት ተወካይ የሆኑት ሻሚሶ ምትሲ የተሀድሶው ርምጃ አዝጋሚ ነው በሚል ወቀሳ ሰንዝረዋል። ምትሲ « ኬ ፒ ሲ ኤስ » ከሕገ ወጡ የአልማዝ ማዕድን ማውጣት ጋ በተያያዘ የሰብዓዊ መብት ረገጣ በሚካሄድባቸው ሀገራት ላይ ጠንካራ ርምጃ እንዲወሰድ ይፈልጋሉ። « ኬ ፒ ሲ ኤስ » በአልማዝ ማዕድናት ፈቃድ አሰጣጥ ላይ ቁጥጥር ማድረግ፣ አስተማማኝ የፀጥታ ሁኔታ መኖሩን፣ ሻጮቹ እና ገዢዎቹን ለይቶ ማወቅ እንደሚጠበቅበት ነው ምትሲ ያመለከቱት። እንደሚታወቀው ፣ ኬ ፒ ሲ ኤስ » ዚምባብዌ የአልማዝ ማዕድንዋን እንድትሸጥ ፈቃድ ሰጥቶዋል፤ ይሁንና፣ ምቲሲ እንደሚሉት፣ ቡድኑ በዚችው ሀገር ማዕድኑ አልማዝ የሚወጣበትን አሰራር በተመለከተ ተጓድሎ ለሚገኘው ግልጽነት እና በኃላፊነት የሚጠየቅ ወገን ትኩረት አልሰጠም።
ይሁንና፣ የደቡብ አፍሪቃ የማዕድን ሚንስትር ሱዛን ሻባንጉ የምትሲን ሀሳብ አይጋሩትም።
« ኬ ፒ ሲ ኤስ » ዚምባብዌም የሚጠበቅባትን ማሟላቷን ካረጋገጥ በኋላ ነው ይህን ሂደት የጀመረው። በተለይ የአውሮጳ ህብረት በዚምባብዌ ላይ የጣለውን ማዕቀብ በማንሳቱም ውሳኔአችን ትክክለኛ ነው ብለን እናምናለን። »
ስብሰባው የፊታችን ዓርብ በሚያበቃበት ጊዜ ደቡብ አፍሪቃ የሊቀመንበርነቱን ሥልጣን ለቻይና ታስረክባለች።

FILE -- In this Wednesday, Nov. 1, 2006 file photo miners dig for diamonds in Marange, eastern Zimbabwe. Zimbabwe's official media says the coalition government has vowed to withdraw troops from the Marange diamond fields and pledged to meet international mining standards. The report Sunday July 5, 2009 follows allegations of human rights abuses and illegal exports of "blood diamonds" from the gem-producing district in the east of the country.(AP Photo/Tsvangirayi Mukwazhi-File)
ምስል AP
The logo of the Antwerp World Diamond Center (AWDC), one of the world's most important diamond-trading centres, is pictured on March 8,2010.
World Diamond Center Antwerpenምስል Getty Images

አርያም ተክሌ

ሸዋዬ ለገሠ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ