ፈንጂ ማምከንና ማፅዳት በአፍሪቃ
ዓርብ፣ መጋቢት 27 2005ማስታወቂያ
በየአመቱ በአለም ዙሪያ በሺህዎችየሚቆጠሩሰዎች በተቀበሩ ፈንጂዎች ህይወታቸው ይጠፋል የአካል ጉዳትም ይደርስባቸዋል ። የዚህ ችግር ግንባር ቀደም ሰለባ ከሆኑት ክፍለ ዓለማት አንዷ አፍሪቃ ናት ። በአፍሪቃ በተቀበሩ ፈንጂዎች ሰብብ የሚደርሰውን ሞትና የአካል ጉዳት ለማስቆም ብቸኛው አማራጭ ሆኖ የተገኘውን ፈንጂዎች ማምከንና የማፅዳቱ ሥራ በስፋት እንደሚቀጥል የአፍሪቃ ህብረት አስታወቋል ። እስካሁን በዚህ ረገድ በአፍሪቃ ስለተከናወነውና ወደፊት ስለታቀደው የፈንጂ ማምከንና ማፅዳት እንቅስቃሴ ጉዳዩ የሚመለከታቸው የአፍሪቃ ህብረት ና የተመድ ሃላፊዎች ትናንት አዲስ አበባ ውስጥ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል ጋዜጣዊ መግለጫውን የተከታተለው የአዲስ አበባው ዘጋቢያችን ጌታቸው ተድላ ኃይለ ጊዮርጊስ ዝርዝር አገባ ልኮልናል ።
ጌታቸው ተድላ ኃይለ ጊዮርጊስ
ሂሩት መለሰ
አርያም ተክሌ