1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ፊሊፒንስ የአውሎንፋስ ተጎጂዎችና ርዳታዉ

ሰኞ፣ ኅዳር 2 2006

ሃኢያን የተሰኘው ከባድ አዉሎነፋስ የፊሊፒንስን ምሥራቃዊ የባህር ዳርቻን ከመታ ዛሬ አራተኛ ቀን ተቆጠረ። የፈራረሱ ቤቶች መተላለፊያ መንገዶችን ዘግተዋል። የስልክ እና የመብራት መስመሮች ተቋርጠዋል።

https://p.dw.com/p/1AFXy
An aerial view of a town devastated by super Typhoon Haiyan in Samar province in central Philippines November 11, 2013. Dazed survivors of super Typhoon Haiyan that swept through the central Philippines killing an estimated 10,000 people begged for help and scavenged for food, water and medicine on Monday, threatening to overwhelm military and rescue resources. REUTERS/Erik De Castro (PHILIPPINES - Tags: DISASTER ENVIRONMENT)
ምስል Reuters/Erik De Castro

ሃኢያን አዉሎነፋስ በፊሊፒንስ እስካሁን ከተከሰቱ የአዉሎነፋስ አደጋዎች እጅግ ከባዱ እንደሆነ ተነግሮለታል። ካለፈው ዓርብ ጀምሮ የሌይቴ አውራጃ የሆነችው ታክሎባን ከተማ ከጥቅም ውጪ ሆናለች። እንደ ፊሊፒንስ መንግሥት ከሆነ 9 ሚሊዮን የሚሆን ህዝብ በአውሎንፋሱ ምክንያት ተጎጂ ሆኗል። ሁሉም ማለት ይቻላል ከህይወት ጋር ትግሉን ተያይዟል።

Residents watch others throw items out from a warehouse after super typhoon Haiyan hit Guiuan town, eastern Samar province, central Philippines November 11, 2013. Dazed survivors begged for help and scavenged for food, water and medicine on Monday, as relief workers struggled to reach victims of a super typhoon that killed an estimated 10,000 people in the central Philippines. REUTERS/Ted Aljibe/Pool (PHILIPPINES - Tags: DISASTER ENVIRONMENT)
ምስል Reuters/Ted Aljibe

ሁሉ ነገር ወድሟል። ምንም የቀረኝ ነገር የለም። ያለኝ ነገር የለበስኩት ልብስ እና የያዝኩት ልጄ ነው» በህይወት የተረፈ እና አቅም ያለው ምግብ እና መጠጥ ካለበት እየዘረፈም ቢሆን ይወስዳል። ይህ አንዳንድ ስልክ ከሚሰራበት አካባቢ የሚመጡ መረጃዎች ናቸው። አሁን ድረስ አንዳንድ የባህር ዳርቻ ላይ ያሉ ቦታዎች ከማንኛውም ርዳታም ይሁን ግንኙነት ተነጥለው ይገኛሉ። ከመዲና ማኒላ እና ከውጭው ሀገራት ፤ የመጠጥ ውሃ፣ መድሀኒት፣ ብርድ ልብስ እና ድንኳን የመሳሰሉ ቁሳቁሶች በርዳታ መልክ ቀርበዋል። ይሁን እንጂ አሁን ድረስ ትልቅ ፈተና የሆነው ፤የተባበሩት መንግሥታት የርዳታ አቀባይ አስተባባሪ ዴቪድ ካርደን እንደሚሉት የመንገድ ችግር ነው።

« ለምሳሌ 6 ሰዓት ያህል ይፈጃል፤ ከአየር ማረፊያው 11 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የሚገኘው ከተማ ለመድረስ።» በየቀኑ አስክሬኖች ይሰበሰባሉ። ከወደሙት ቤቶች ስር በህይወት ያሉ ሰዎችን የማግኘት እድሉ ቀናት በተቆጠሩ ቁጥር እየቀነሰ መጥቷል። ፍለጋው ግን እንደቀጠለ ነው። እንደ ጀርመን ያሉ የውጭ ሀገራት የቁሳቁስ ድገፋ ብቻ ሳይሆን የሰው ኃይልም ወደ አካባቢው እየላኩ ይገኛሉ። «ቴሽኒሸ ሂልፍስቬርክ» የተሰኘው የጀርመን የሲቪል እና የአደጋ ጊዜ ደራሽ ድርጅት፤ መርማሪ ቡድኑን ማኒላ ካደረሰ ድርጅት አንዱ እንደሆነ የድርጅቱ ቃል አቀባይ ኒኮላስ ሄፍነር ለዶይቸ ቬለ ገልጸዋል። እሳቸው እንደሚሉት ከሀገሪቱ መስሪያ ቤቶች ጋ በመተባበር የርዳታ ስርጭቱን ማቀድ አስፈላጊ ነው።

Residents rush to a military helicopter to get food packs during a relief distribution after super typhoon Haiyan hit Iloilo province, central Philippines November 11, 2013. Dazed survivors of a super typhoon that swept through the central Philippines killing an estimated 10,000 people begged for help and scavenged for food, water and medicine on Monday, threatening to overwhelm military and rescue resources. REUTERS/Leo Solinap (PHILIPPINES - Tags: DISASTER ENVIRONMENT)
ምስል Reuters/Leo Solinap

« የአስተባባሪነቱን ዋና ኃላፊነት የሚወስዱት ፊሊፒያኖቹ ናቸው። ማኒላ የአውሎንፋሱ ተጎጂ ባለመሆኗ የአደጋ ጊዜ ደራሽ መስሪያ ቤቶቹ በሙሉ አገልግሎት በመስጠት አቅም ላይ ነው ያሉት። እንደሰማሁት ብዙ ወታደሮች እና ፖሊሶች አደጋው ወደደረሰባቸው አካባቢዎች ተልከዋል። ስለዚህ ብቻችንን ሆነን መወሰን ያለብን ርምጃ የለም። »

በሚመጡት ቀናት ማንኛውም የርዳታ አይነቶች ወሳኝ ናቸው ይላሉ። የተባበሩት መንግሥታት የርዳታ አቀባይ አስተባባሪ ካርደን፤ የአውሮፓ ኮሚሽን 3 ሚሊዮን ዮሮ ርዳታ መፍቀዱን ተናግሯል። የዮናይትድ ስቴትስ ኤምባሲ 75000 ዮሮ አፋጣኝ ርዳታ፣ የጀርመን መንግሥት እንዲሁ ግማሽ ሚሊዮን ዮሮ አፋጣኝ ርዳታ ፈቅዷል። የፊሊፒንስ ፕሬዚዳንት ቤኒግኖ አቁኖ አደጋው ወደደረሰበት አካባቢ ሄደው የታዘቡትን እንደሚከተለው ነው የገለፁት።

« ብዙ የጠፉ ሰዎች መኖራቸው ያሳዝናል። እስካሁን መሞታቸው የተረጋገጠውም በርካታ ሰዎችም እንዲሁ። አሁን ግን በተለይ በህይወት ለተረፉት ነው ትኩረታችን። በተለይም የቆሰሉት ምግብ እና ውሃ ያስፈልጋቸዋል።» 600 ኪሎ ሜትር ስፋት የነበረው ሃኢያን ከባድ አዉሎነፋስ በሰው እና በንብረት ላይ ያስከተለው ጥፋት ከቀን ወደ ቀን እየጨመረ ይገኛል።

ልደት አበበ

አርያም ተክሌ