1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ፔን እስክንድር ነጋን ሸለመ

ዓርብ፣ ጥቅምት 12 2008

ሽልማቱን በየዓመቱ የሚያበረክተው በጽሁፎቻቸው በሚያነሷችው ሀሳቦች ድንበር ሳያግዳቸው በተለያየ ባህል እና ወግ ውስጥ የሚኖረውን ኅብረተሰብ ማስተሳሰር ለቻሉ ፀሀፍት አልያም ጋዜጠኞች ነው።

https://p.dw.com/p/1GtMB
Symbolbild Organsiation
ምስል Colourbox

[No title]

መቀመጫውን በቶሮንቶ ካናዳ ያደረገው ፔን ካናዳ የተባለ ለፍትና ጋዜጠኞች መብት የሚሟገት ድርጅት በኢትዮጵያ በእስር ላይ ለሚገኘው ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ «one humanity award» የተባለውን ሽልማት እንደሚያበረክት ገለጸ። ሽልማቱም 5 ዶላር ዋጋ አለው ተብሏል። ፔን ካናዳ 148 የፔን ለም አቀፍ ከላት መካከል አንዱ ሲሆን ሽልማቱን በየመቱ የሚያበረክተው በጽሁፎቻቸው በሚያነሷችው ሀሳቦች ድንበር ሳያግዳቸው በተለያየ ባህል እና ወግ ውስጥ የሚኖረውን ብረተሰብ ማስተሳሰር ለቻሉ ሀፍት አልያም ጋዜጠኞች ነው። በጎርጎሮሳዊው ከታህሳስ 22 እስከ ህዳር 1 ቀን 2015 በሚቆየው 36ኛው ለም አቀፍ ሀፍት ፌስቲቫል ላይ ነው «ፔን ካናዳ» ሽልማቱን ለታሳሪው ጋዜጠኛ የሚያበረክተው። የፔን ኢትዮጵያ ተወካዮች እስክንድርን በመወከል ሽልማቱን ይቀበላሉም ተብሏል። ናትናኤል ወልዴ ከዋሽንግተን ዲሲ ተጨማሪ ዘገባ ለኮልናል።

ናትናኤል ወልዴ

አዜብ ታደሰ