5 ታራሚዎች በእሳት መንስኤ መሞታቸው
ሰኞ፣ ታኅሣሥ 15 2005ማስታወቂያ
ምሥራቅ ጎጃም ደብረ ማርቆስ በሚገኝ አንድ እስር ቤት ባለፈው አርብ እኩለ ለሊት በደረሰ የእሳት አደጋ የ 5 ታራሚዎች ህይወት ሲያልፍ ከ16 የማያንሱ ደግሞ ቀላልና ከባድ ጉዳት እንደደረሰባቸው የአይን ምስክሮች ተናገሩ ። የማረሚያ ቤቱ ሃላፊ ግን በአደጋው የሞቱት 5 መሆናቸውን አረጋግጠው የቆሰሉት ግን 16 ሳይሆኑ 5 ናቸው ብለዋል ። ሃላፊው ታራሚዎቹ የሞቱትም በእሳት ቃጠሎ ሳይሆን በዚያ ሰበብ በተፈጠረው ግርግር ምክንያት ነው ሲሉ ለዶቼቬለ ተናግረዋል ። ዝርዝሩን ዮሐንስ ገብረ እግዚአብሔር ከአዲስ አበባ ልኮልናል ።
ዮሐንስ ገብረ እግዚአብሔር
ሂሩት መለሰ
ነጋሽ መሐመድ