1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

CPJ-አሳሳቢዉ የጋዜጠኞች መብት ጥሰት

ማክሰኞ፣ ነሐሴ 7 2005

ለጋዜጦች መብት የሚሟገተዉ ድርጅት CPJ በኢትዮጵያ ዉስጥ በጋዜጠኞች ላይ እየተወሰደ ያለዉ እርምጃ እንዳሳሰበዉ ገለጸ።

https://p.dw.com/p/19On7
Logos des "Committee to Protect Journalists" (www.cpj.org), eine weltweit agierende NGO mit Sitz in New York, die für den Schutz von Journalisten und für Pressefreiheit kämpft.

ተቋሙ ሰሞኑን ሁለት ጋዜጠኞች ለእስራት መዳረጋቸዉ በፕሪስ ነፃነት ላይ የተደረገ ጥቃት ነዉ ሲል ገልጾአል። የዋሽንግተን ዲሲዉ ወኪላችን አበበ ፈለቀ ዘገባ ልኮልናል። ዓለማቀፉ የጋዜጠኞች መብት ተከላካይ ኮሚቴ CPJ፤ ሁለት ጋዜጠኞች ከሁለት ሳምንታት በላይ ያለክስ መታሰራቸዉ እንዳሳሰበዉ ነዉ የገለፀዉ። የተቋሙ የአፍሪቃ ጉዳዮች አስተባባሪ መሃመድ ኬዬታ፤ የነዚሁ ጋዜጠኞች እስራትን በተመለከተ እንደተናገሩት « በሐምሌ 26 ቀን የኢትዮጵያ የደህንነት ኃይሎች ለራድዮ ቢላል የሚሰሩትን ሁለት ጋዜጠኞች፤ ደርሴማ ሶልንና፤ ካሊድ ሞሃመድን አስረዋቸዋል። የሙስሊም ፀረ- መንግስት ተቃዎሞ የዜና ሽፋን ሲሰጡ ነበር። እናም በደህንነት ሃይሎች ተይዘዉ አዲስ አበባ በፖሊስ ጣብያ ዉስጥ በእስር ላይ ይገኛሉ»



አበበ ፈለቀ
አዜብ ታደሰ
ሒሩት መለሰ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ