Eshete Bekeleቅዳሜ፣ ግንቦት 3 2016በኢትዮጵያ የ12ኛ ክፍል ፈተና ከሐምሌ 3 እስከ 12 ቀን 2016 ሊሰጥ ነው። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ቀሪ ምርጫ በሚደረግባቸው ቤኒሻንጉል ጉሙዝ እና አፋር ክልሎች፤ ድጋሚ ምርጫ በሚደረግባቸው በጅግጅጋ 2 እና መስቃን እና ማረቆ ምርጫ ክልሎች የዕጩዎችን ምዝገባ እስከ ሐምሌ 6 ቀን 2016 አራዘመ። በአፍጋኒስታን ሦስት ግዛቶች በደረሰ የጎርፍ አደጋ የሞቱ ሰዎች ቁጥር 153 መድረሱን የሀገሪቱ መንግሥት አስታወቀ። የጸጥታ ጥበቃው ምክር ቤት በጋዛ ሁለት ሆስፒታሎች በተገኙ የጅምላ መቃብሮች ላይ ምርመራ እንዲደረግ ጥሪ አቀረበ። እስራኤል ራፋሕን ጨምሮ በጋዛ የተለያዩ አካባቢዎች ዛሬ ቅዳሜ ኃይለኛ ድብደባ ፈጽማለች።