1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

DW Amharic የግንቦት 03 ቀን 2016 የዓለም ዜና

Eshete Bekeleቅዳሜ፣ ግንቦት 3 2016

በኢትዮጵያ የ12ኛ ክፍል ፈተና ከሐምሌ 3 እስከ 12 ቀን 2016 ሊሰጥ ነው። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ቀሪ ምርጫ በሚደረግባቸው ቤኒሻንጉል ጉሙዝ እና አፋር ክልሎች፤ ድጋሚ ምርጫ በሚደረግባቸው በጅግጅጋ 2 እና መስቃን እና ማረቆ ምርጫ ክልሎች የዕጩዎችን ምዝገባ እስከ ሐምሌ 6 ቀን 2016 አራዘመ። በአፍጋኒስታን ሦስት ግዛቶች በደረሰ የጎርፍ አደጋ የሞቱ ሰዎች ቁጥር 153 መድረሱን የሀገሪቱ መንግሥት አስታወቀ። የጸጥታ ጥበቃው ምክር ቤት በጋዛ ሁለት ሆስፒታሎች በተገኙ የጅምላ መቃብሮች ላይ ምርመራ እንዲደረግ ጥሪ አቀረበ። እስራኤል ራፋሕን ጨምሮ በጋዛ የተለያዩ አካባቢዎች ዛሬ ቅዳሜ ኃይለኛ ድብደባ ፈጽማለች።

https://p.dw.com/p/4fkFD
ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ከዚሕ ዝግጅት ተጨማሪ

ከዚሕ ዝግጅት ተጨማሪ

Äthiopien Alamata City Gondar
ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ስለዚሕ ዝግጅት

ስለዚሕ ዝግጅት

PODC-DW-Amharisch-News-DWcom

የዓለም ዜና

ዶይቼ ቬለ የዕለቱን ዋና ዋና የዜና ትንታኔዎች ከኢትዮጵያ እና ከመላው ዓለም በየቀኑ ያቀርባል። የኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ፖለቲካዊ እና ኤኮኖሚያዊ ጉዳዮችን ጨምሮ የመላው ዓለምን ውሎ የተመለከቱ ጠቃሚ መረጃዎች በሰባቱም የሣምንቱ ቀናት ከምሽቱ አንድ ሰዓት ከዶይቼ ቬለ ያድምጡ።