1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የአፍሪቃ ኅብረት እና የአውሮጳ ኅብረት ስብሰባ

ዓርብ፣ ኅዳር 8 2010

የአፍሪቃ ኅብረት እና የአውሮጳ ኅብረት በሠላም እና በጸጥታ ጉዳዮች ላይ  የጀመሩትን የጋራ ሥራ ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር  ስምምነት ላይ ደርሰዋል።  

https://p.dw.com/p/2nphy
Äthiopien - Mahamat Zene in Addis Abeba
ምስል DW/G. Tedla HG

EU-AU cooperation on Peace & Security - MP3-Stereo

የአፍሪቃ ኅብረት እና የአውሮጳ ኅብረት በሠላም እና በጸጥታ ጉዳዮች ላይ  የጀመሩትን የጋራ ሥራ ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር  ስምምነት ላይ ደርሰዋል።  የአፍሪቃ ኅብረት የሰላምና ጸጥታ ምክር ቤት ከአውሮጳ ኅብረት የፖለቲካ እና ደህንነት ኮሚቴ ጋር በጋራ በሚያከናው 10ኛው የምክክር ጉባኤ ላይ  የስደተኞች ጉዳይና በግጭት የፈረሱ መሰረተ ልማቶችን መልሶ ማቋቋም ጉዳይ ትኩረት ተሰጥቶታል።  በአፍሪቃ ኅብረት አዳራሽ ትናንት የጀመረው ውይይት የሚጠናቀቀው በነገው እለት ነው። የአዲስ አበባው ወኪላችን ጌታቸው ተድላ ኃይለ ጊዮርጊስ ጉባኤውን ተከታትሎ ቀጣዩን ዘገባ አጠናቅሮልናል። 

ጌታቸው ተድላ ኃይለ ጊዮርጊስ
ማንተጋፍቶት ስለሺ
ኂሩት መለሰ