ተሰናባቹና አዲሱ የዉጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባዮች
ዓርብ፣ ጥር 3 2011ማስታወቂያ
የዉጭጉዳይ ሚኒስቴር ባደረገዉ የመዋቅር ማሻሻያ መሠረት ፤ የቀድሞዉ ቃል አቀባይ አቶ መለስ ዓለም በኬንያ ናይሮቢ የኢትዮጵያ አምባሳደር ሆነዉ የተመደቡ ሲሆን የመጨረሻዉን መግለጫ በዉጭ ጉዳይ መስሪያቤት የስብሰባ አዳራሽ ሰጥተዋል። አቶ መለስን ተክተዉ የኢትዮጵያ የዉጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ሆነዉ የተሾሙት አቶ ነብያት ጌታቸዉ ከጋዜጠኞች ጋር ትዉዉቅ አድርገዋል። የኢትዮጵያ አብማሳደር ሆነዉ ለተለያዩ ሃገራት የተመደቡት ከስድሳ በላይ አምባሳደሮች የመጨረሻዉን ዉይይት እና ስንብት የፊታችን ሰኞ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ጋር ያደርጋሉ ተብሎአል። ዝርዝሩን የአዲስ አበባዉ ወኪላችን ልኮልናል።
ጌታቸዉ ተድላ ኃይለ ጊዮርጊስ
አዜብ ታደሰ
አርያም ተክሌ