1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ዴንማርክ፤ የአይሁዳዊያን ምኩራብ ፊት ለፊት ተኩስ

እሑድ፣ የካቲት 8 2007

ኮፕንሐግን በሚገኝ አንድ የአይሁዳዊያን ፀሎት ቤት ፊት ለፊት ቅዳሜ ለእሁድ አጥቢያ በተከፈተ ተኩስ ቢያንስ ሦስት ሰዎች ቆሰሉ። የዴንማርክ ፖሊስ እንዳስታወቀው ከቁስለኞቹ መካከል ሁለቱ ፖሊሶች ናቸው። ይህ ከሆነ ከሰዓታት በኋላ ፖሊስ በእግሩ እንደሸሸ የተነገረውን ተጠርጣሪ ማግኘቱን እና መግደሉን ይፋ አድርጓል።

https://p.dw.com/p/1Ec8r
Dänemark Kopenhagen Schießerei Blasphemie Debatte
ምስል picture alliance/Scanpix Denmark/M. OEgendal

እንደ ፖሊስ ገለፃ ተጠርጣሪው የአይሁዳዊያን ምኩራብን ሲጠብቅ ለነበረ ወጣት ሞት ተጠያቂ ነው። ከዚህም በተጨማሪ በፖሊስ የተገደለው ተጠርጣሪ ይህ ከመሆኑ ከሰዓታት በፊት በአንድ ስብሰባ ላይ የተካፈሉ የ55 ዓመት ሰውንም ሳይገድል አልቀረም ተብሏል። በስብሰባው ላይ የተከፈተው ተኩስ ምናልባትም ኢላማ አድርጎ የነበረው ላርስ ቪልክስ የተባሉ የስላቅ ስእሎች ሰዓሊ ላይ ሳይሆን እንዳልቀረ ፖሊስ ገልጿል። ስዊዲናዊው ሰዓሊ ነብዩ መሐመድን የሚመለከቱ ስላቃዊ ምስሎችን ይስላሉ በሚል በተደጋጋሚ በሙስሊሞች ዘንድ ወቀሳ ቀርቦባቸው እና የጥቃት ኢላማም ሆነው እንደነበር ተገልጿል።

ልደት አበበ

ማንተጋፍቶት ስለሺ