1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ሀገር አቀፍ ምርጫ በጀርመን-ዉይይት

እሑድ፣ መስከረም 12 2006

የጀርመን ፖለቲከኞች አሸንፈው ምክር ቤት ለመግባት ከፍተኛ የምረጡኝ ዘመቻና ክርክር ሲያደርጉ ሠንብተዋል። የሜርክል ፓርቲ አሸንፏል።እንዴት?

https://p.dw.com/p/19lgY
አንጌላ ሜርክልና ፒር ሽታይንብሩክ በምርጫ ዘመቻ
አንጌላ ሜርክልና ፒር ሽታይንብሩክ በምርጫ ዘመቻምስል imago stock&people

ዲሞክራሲ በሰረፀባቸው የዓለማችን ክፍሎች ምርጫ፦ ሥልጣን ሠላማዊ በሆነ መንገድ ሽግግር የሚደረግበት ሂደት ነው። በአንፃሩ ዲሞክራሲ የሠማይ መንገድ ያህል በራቀባቸው ሃገራት ደግሞ ይኸው ምርጫ፤ አብላጫውን ጊዜ የውዝግብ፣ የመጠላለፍና የመጠፋፋት ወጥመድ ሲሆን ይስተዋላል። ዲሞክራሲ አብቦባቸዋል ከሚባሉ የዓለማችን ጥቂት ሃገራት መካከል ጀርመን አንዷ ናት። የዛሬው የውይይት መድረክ ዝግጅታችን «የፌዴራል ጀርመን የምክር ቤት ምርጫ ምንነት፣ አንድምታ እና አስተምኅሮቱ» የሚል አቢይ ርዕስ ይዟል። ለውይይቱ ሶስት እንግዶችን ጋብዘናል። ዶ/ር ለማ ይፍራሸዋ በጀርመን ሀገር ለረጅም ጊዜ የኖሩ እዚሁ ጀርመንም የተማሩ የሕግ ባለሙያና የፖለቲካ ሣይንስ ምሁር፤ ሌላኛው የውይይቱ ተሳታፊ የፌደራል ጀርመን ዋነኛ ፖለቲከኞች ማዕከል በሆነችው በርሊን ከተማ ውስጥ ነዋሪ የሆነው ወኪላችን ይልማ ኃይለሚካኤል ነው። የአውሮጳ ኅብረት መቀመጫ ከሆነችው ከቤልጂየም ብራስልስ የአውሮጳ ፖለቲካን በቅርበት የሚከታተለው ሌላኛው ወኪላችን ገበያው ንጉሤም በውይይቱ ይሳተፋል።

ማንተጋፍቶት ስለሺ

አዜብ ታደሰ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ