1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ሊቢያና ያልተሳካው የአፍሪቃ ኅብረት ሽምግልና፣

ማክሰኞ፣ ግንቦት 23 2003

የደቡብ አፍሪቃው ፕሬዚዳንት ጄኮብ ዙማ፤ የአፍሪቃ ኅብረትን የሽምግልና ሐሳብ፣ ለሊቢያው መሪ ኮሎኔል ሙኧመር ጋዳፊ ትሪፖሊ ድረስ በመጓዝ ቢያቀርቡም፣ ሽምግልናው ሳይሠምር ነው የቀረው።

https://p.dw.com/p/RR3r
ምስል dapd

የአፍሪቃ ኅብረት ፣ በመንግሥት ወታደሮችና በአማጽያን መካከል 3 ወራት ገደማ የሆነው ውዝግብ ወይም የተኩስ ልውውጥ፣ የኔቶ የአየር ድብደባ ጭምር ባስቸኳይ እንዲቆም ነበረ የጠየቀው። ውዝግቡን በእርግጥ በሰላማዊ መንገድም ሆነ በዲፕሎማሲ ለመፍታት ዕድሉ አሁንም አለ ማለት ይቻላል? ተክሌ የኋላ፣ በፕሪቶሪያ የዓለም አቀፉ ስልታዊ ጥናት ተቋም ስራ አስኪያጅ የሆኑትን ጃኪ ሲልየርስን አነጋግሮ የሚከተለውን ዘገባ አጠናቅሯል።

የአፍሪቃን ኅብረት የሰላም ሐሳብ ይዘው ነበረ ፕሬዚዳንት ጄኮብ ዙማ ወደ ትሪፖሊ ጎራ ያሉት። የሊቢያው መሪ ፤ ተኩስ ቆሞ፣ ውይይት እንዲጀመር የቀረበውን የሰላም ሐሳብ ቢቀበሉትም፤ ከአማጽያኑ አሁንም በጎ ምላሽ ያገኘ አይመስልም። ከእንግዲህ ውዝግቡን በሰላም ለመፍታት የዲፕሎማሲው ጥረት አክትሟል ወይስ ሌላ ዕድል ይኖራል? ጃኪ ሲልየርስ--

«ፕሬዚዳንት ዙማ፤ የአፍሪቃን ኅብረት ወክለው ነው በሊቢያ የተገኙት። ከውዝግቡ መላቀቅ የሚቻልበትን መላ ለመሻት!በግልጽ እንደሚታየው፣ የአየር ድብደባው በራሱ ጋዳፊን ከሥልጣን የሚያፈናቅል አይደለም እንደሚመስለኝ ለሆነ የሰላም ሂደት፣ ድጋፉ እየጨመረ በመሄድ ላይ ሲሆን፤ ይህ የሚንቀሳቅስበትን በር ክፍቷል። ፕሬዚዳንት ዙማም ይህን መነሻ አድርገው ነው በዚያ የተገኙት።»

ለመሆኑ፤ ጋዳፊ ውሎ-አድሮ አስተማማኝ ሁኔታ ከተገኘ አገር ጥለው ምናልባት ወደ ደቡብ አፍሪቃ የሚሰደዱ ይመስሎታል?

ተክሌ የኋላ

መሳይ መኮንን

ሸዋዬ ለገሰ