1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ሊቢያ እና ምክር ቤታዊው ምርጫ

ሰኞ፣ ሐምሌ 2 2004

ሊቢያውያን ሀገሪቱን ለአርባ ሁለት ዓመታት የገዙት የቀድሞው መሪ ሞአመር ኧል ጋዳፊ በሕዝብ ዓመፅ ከተወገዱ ወዲህ ባለፈው ቅዳሜ የብሔራዊ ምክር ቤት እንደራሴዎቻቸውን የመረጡ ሲሆን ፡ ሀገሪቱ ወደዴሞክራሲያዊው ሥርዓት ለመሸጋገር በያዘችው ሂደት ላይ ይህ የመጀመሪያው ርምጃ ሆኖ አግኝተውታል፤

https://p.dw.com/p/15Ty5
High National Election Commission workers check ballot boxes after collecting them from different polling stations as they prepare for the final count, in Benghazi July 8, 2012. Nine months after Muammar Gaddafi's death at the hands of rebels, Libya has defied fears it would descend into violence by pulling off a largely peaceful election, its first national and free vote in 60 years. REUTERS/Esam Al-Fetori (LIBYA - Tags: POLITICS ELECTIONS)
ምስል Reuters

ይሁንና፡ ይኸው የመጀመሪያ ነፃ የምርጫ ሂደት በሀገሪቱ በቀጠለው የጎሳ ግጭትና ሕዝብ ከምርጫ እንዲርቅ በቀረበ ጥሪ ጥላ አጥሎበታል። ለሞአመር በአርባ ዓመቱ የጋዳፊ አመራር ዘመን ምክር ቤትም ሆነ ሕገ መንግሥት አልነበረም። የፖለቲካ ፓርቲ ምሥረታምም ሆነ አባልነት በሞት ያስቀጣም ነበር። ዎች ጋዳፊ ከተገደሉ ከዘጠኝ ወራት በኋላ ሊቢያውያን ድምፃቸውን እንዲሰጡ መጠራታቸውን እንደ አዲስ ክስተት ነው የተመለከቱት። የመምረጥ መብት ያላቸው 2,8 ሚልየን ሊቢያውያን ሁለት መቶ መንበሮች ለሚኖሩት ምክር ቤት በተፎካካሪነት ከቀረቡ 3,800 ዕጩዎች እና ከ 140 ፓርቲዎች መካከል መምረጥ ይችላሉ። ግን በሀገሪቱ ዴሞክራሲያው ባህል ባለመኖሩ፡ ለብዙ መራጮች ድምፅ በሚሰጡበት ውሳኔአቸው ላይ ተወዳዳሪ ዕጩዎች ከየትኛው አካባቢ ወይም ጎሳ መጡ የሚለው ጉዳይ እንጂ የሚከተሉት የፖለቲካ ፕሮግራማቸው ትርጉም እንደሌለው የሊቢያን ፖለቲካ በቅርብ የሚከታተሉ የፖለቲካ ተንታኞች ገልጸዋል።
አዲስ የሚመረጠው ብሔራዊ ምክር ቤት ሀገሪቱን በጊዚያዊነት የሚያስተዳድር የሽግግር መንግሥት ያቋቁማል፤ ሕገ መንግሥታዊውን ምክር ቤትም ይሠይማል። ከዚያ መራጩ ሕዝብ ወደፊት በሚካሄደው ሁለተኛ ምርጫ በሚረቀቀው ሕገ መንግሥት ላይ ድምፁን ይሰጣል ። በነዳጅ ዘይት የተፈጥሮ ሀብት ለታደለችውና በአምባገነን ሥርዓት ሥር ለቆየችው ሰሜን አፍሪቃዊቱ ሀገር ልትወጣው የምትገባ ትልቅ ፈታኝ ሁኔታ ነው። ሀገሪቱ በተለያዩ አካባቢዎች በተቀናቃኝ ቡድኖች፡ ባማፅያን ሚሊሺያዎችና በጎሳዎች መካከል በሚካሄዱ ግጭቶች አሁንም አሳሳቢ ችግር የተደቀነባት ሲሆን፡ በምሥራቃዊው የሀገሪቱ ከፊል የሚንቀሳቀሱ አንዳንድ ኃይላት ሕዝቡ በዛሬው የብሔራዊ ምክር ቤት ምርጫ እንዳይሳተፍ የተጠናከረ ጥሪ ሲያስተላልፉ ነው የቆዩት። ሊቢያን በወቅቱ የሚያስተዳድረው የሽግግሩ ምክር ቤት የፀጥታው ጥበቃ ከቁጥጥር እንዳይወጣ ከፍተኛ ጥረት በማድረግ ላይ ቢገኝም፡ በብዙ የሀገሪቱ አካባቢዎች አሁንም ከባድ ውጊያ እንዳለ ነው የሚሰማው፤ በተለይ ብዙ የጦር መሣሪያ የሚዘዋወርበት ድርጊት ሁኔታውን አዳጋች አድርጎታል።
አርያም ተክሌ

epa03299131 Libyans celebrate the vote in the National Congress elections at the corniche road (seaside road), in Benghazi, Libya, 07 July 2012. Voters headed to the polls across Libya on 07 July to elect a 200-seat National Congress, which will have legislative powers and appoint a new government, amid fears of violence and calls for boycott in eastern cities. Around 2.7 million Libyans have registered to vote to elect the assembly, consisting of 120 directly elected members and 80 contenders from party lists. EPA/AMEL PAIN +++(c) dpa - Bildfunk+++
ምስል picture-alliance/dpa

መሥፍን መኮንን