1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ሙስና እና የእስር ዘመቻ

እሑድ፣ ሐምሌ 30 2009

ኢትዮጵያ መንግስት ካለፈው ሳምንት ወዲህ በሙስና ተጠርጥረዋል ያላቸውን የመንግሥት ኃላፊዎች እና ባለሀብቶችን አስሯል። አሁን ቁጥራቸው 50 ከደረሰው የታሰሩት የመንግሥት ሰራተኞች  መካከል  ብዙ ከፍተኛ የሚባሉ ይገኙባቸዋል።

https://p.dw.com/p/2hikk
Geldscheine
ምስል DW/E. Bekele Tekle

የፌደራል እና አዲስ አበባ መንገዶች ባለስልጣን፣ የገንዘብ እና ኤኮኖሚ ትብብር ሚኒስቴር፣ የአዲስ አበባ ቤቶች ልማት ፕሮዤ ጽህፈት ቤት እና የስኳር ኮርፖሬሽን  ኃላፊዎች የመታሰር እጣ ገጠማቸው መካከል ይጠቀሳሉ። የዛሬው ውይይት መንግሥት በሀገር ልማት ላይ ትልቅ እንቅፋት ደቅኗል ባለው ሙስና አንጻር ሰሞኑን እየወሰደ ባለው ርምጃ ላይ  ያተኩራል።

አርያም ተክሌ

ልደት አበበ