1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ሜሢ ለ4ኛ ጊዜ ምርጥ ተጫዋች ተባለ

ማክሰኞ፣ ታኅሣሥ 30 2005

አርጀንቲናዊው እውቅ እግር ኳስ ተጫዋች ሊዮኔል ሜሢ ለ4ኛ ጊዜ ምርጥ የአመቱ የአለም እግር ኳስ ተጫዋች በመሆን ተመረጠ። ከሴቶች ደግሞ የዮኤስ አሜሪካ አጥቂ ተጫዋች አቢ ቫምባህ ምርጥ ተጫዋች ተብላለች።

https://p.dw.com/p/17GAk
Lionel Messi of Argentina, FIFA World Player of the Year 2012 holds his FIFA Ballon d'Or trophy during the FIFA Ballon d'Or 2012 soccer awards ceremony at the Kongresshaus in Zurich January 7, 2013. REUTERS/Michael Buholzer (SWITZERLANDSPORT SOCCER - Tags: SPORT SOCCER HEADSHOT)
ምስል Reuters

የዓለም እግር ኳስ ፌዴሬሽን በምህጻሩ ፊፋ እአአ በ2009 , 2010 እና 2011 ዓ ም የአመቱ ምርጥ ተጫዋች አድርጎ የመረጠውን የስጳኛውያኑ የእግር ኳስ ቡድን - የኤፍሲ ባርሴሎና አጥቂ ተጫዋች ሊዮኔል ሜሲን ዘንድሮም እንደገና የአለም ምርጥ እግር ኳስ ተጫዋች ሲል በድጋሚ ሰይሞታል። ይህም የ25 አመቱን ወጣት ብቸኛ ባለ ክብረ ወሰን ጠባቂ አድርጎታል።

MADRID, SPAIN - AUGUST 29: (Back row L-R) Pedro Rodriguez, Javier Mascherano, Sergio Busquets, Gerard Pique, Victor Valdes (Front row L-R) Lionel Messi, Alexis Sanchez, Adriano Correia, Andres Iniesta, Xavi Hernandez, Jordi Alba of FC Barcelona pose for a team picture prior to the Super Cup second leg match betwen Real Madrid and FC Barcelona at Estadio Santiago Bernabeu on August 29, 2012 in Madrid, Spain. (Photo by David Ramos/Getty Images)
ምስል Getty Images

ሊዮኔል ሜሢ የቡድኑን ባልደረባ አንድሬ ኢኒስታ እና ፖርቱጋላዊውን የ ሪያል ማድሪድ ተጫዋች ክሪስቲያኖ ሮናልዶን በመብለጥ ለ4ኛ ጊዜ «ምርጥ የእግር ኳስ ተጫዋች» ተብሎ በመመረጥ በኳስ የተመሰለውን የወርቅ ሽልማት ተቀብሏል። « ረጋ ብዬ በሁኔታው እየተደሰትኩ ነው። » ነው ያለው ሜሢ ። ሽልማቱ የተሰጠው ጋዜጠኞች፣ ታዋቂ የእግር ኳስ እጩዎች እና የብሔራዊ ቡድን አሰልጣኞች በተሰበሰቡበት ነው። 23 የእግር ኳስ እጩዎች ያካተተው የአለም እግር ኳስ ፌደሬሽን -ፊፋ መዘርዝር ላይ በእጩነት ለጀርመን ብሔራዊ ቡድን የሚጫወቱት ማኑኤል ኖየር - ከባየር ሙኒክ እና ሜሱት ኦዚል - ከሪያል ማድሪድ ይገኙበታል። ይሁንና ሌሎች ሁለት ጀርመንያውያን እጩ ተጫዋቾችን ጨምሮ ማንኛቸውም ለሽልማቱ ሊበቁ አልቻሉም።ስለሆነም ብቸኛው የጀርመን ባለክብረወሰን ሎታር ማቲዎስ እኢአ 1990 እና 1991 ዓም ሆኖ ይቆያል።

የባየር ሌቬርኩዝን ተጫዋች እስቴፋን ራይንአርትስት ፤ ሌቨርኩዝን ሰባት ለአንድ በባርሴሎና ሲሸነፍ ራይንአርትስት ስለ ሚሢ እንዲህ ነበር ያለው። «አስገራሚ ነው። አንዳንዴ ምንም ሳይካፈል በኳስ ሜዳ ይቆማል። ማንም ይጫወት እና ኳስ ይደርሰዋል ብሎ እንኳን አይገምትም። ከዛ ባንዴ ከምንም ውስጥ ብቅ ይላል።»

ZURICH, SWITZERLAND - JANUARY 07: Real Madrid's Portuguese forward Cristiano Ronaldo, Real Madrid's Marcello, Real Madrid's Sergio Ramos, Barcelona's Gerard Pique, Barcelona's Dani Alves, Real Madrid's Iker Casillas (Bottom L-R) Atletico Madrid's Colombian forward Radamel Falcao, Barcelona's Argentinian forward Lionel Messi, Barcelona's Spanish midfielder Andres Iniesta, Barcelona's Xavi Hernandez and Real Madrid's Xabi Alonso receive the FIFA/FIFPro World XI award during the FIFA Ballon d'Or awards ceremony at the Kongresshaus in Zurich on January 7, 2013. (Photo by Christof Koepsel/Getty Images)
ምስል Getty Images

የሜሢ የ4ኛ ጊዜ መመረጥ የዮናይስት እስቴት የሴቶች አጥቂ የእግር ኳስ ተጫዋች -አቢ ቫምባህ ባለድልነትን ጎልቶ እንዳይወጣ ያድርግ እንጂ፤ ቫምባህ ዮኤስ አሜሪካ በለንደን በነበራት የኦሎምፒክ ግጥሚያ አምስት ግብ በማስቆጠር ብቸኛ ተጫዋች ነበረች። የ 32 አመቷ አሜሪካዊት ቅፅል ስሟም ቦምቧ የሚል ነበር። ቫምባህ የቡድን ባልደረባዋን አሌክስ ሞርጋን እና የብራዚል ኮከብ ተጫዋች ማርታን በመቅደም አሸናፊ ሆናለች። ማርታ አምስት ጊዜ የዚህ የአለም ምርጥ እግር ኳስ ተጫዋች ሆና መቆየቷ የሚታወስ ነው። እኢአ ከ 2001-2002 ክብረ ወሰኑን ይዛ ከነበረችው -ሚያ ሃም- በኋላ ቫምባህ ሌላኛዋ ዮ ኤስ አሜሪካዊት መሆኗ ነው።

በሌላ ዜና የ 2012 ምርጥ የአለም አሰልጣኝ በመሆን የስፓኝ ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ ቪንሴንቴ ዴል ቦስክ ተመርጠዋል። በሴት አሰልጣኝነት ደግሞ ፒያ ሰንዳጌ ተመርጣለች። ሲውዲናዊትዋ አሰልጣኝ የኤስ አሜሪካ ቡድን ለንደን በተካሄደው ጨዋታ የወርቅ ሜዳሊያ ተሸላሚ እንዲሆን ትልቅ ሚና ተጫውታለች።

የፊፋ ፕሬዚዳንትነትን ሽልማት በማግኘት የክብር ተሸላሚ የሆኑት ጀርመናዊው ፍራንስ ቤክንባወርም አንድ በኳስ የተመሰለ የወርቅ ኳስ ባለቤት ሆነዋል። የእግር ኳስ አድናቂዎች በሰጡት ድምፅ ደግሞ ቱርካዊው ሚሮስላቭ እስቶኽ ያመቱን ምርጥ ግብ ከመርብ ያገናኘ ተጫዋች በማለት መርጠውታል።

አንድሪያስ እስቴን ዚሞንስ

ልደት አበበ

አርያም ተክሌ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ