1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ሜዲቴራንያን ላይ የወደቀው የኢትዮጵያ አውሮፕላን

ሰኞ፣ ጥር 17 2002

ትናንት ከለሊቱ ስምንት ሰዓት ተኩል ከሊባኖስ ዋና ከተማ ከቤይሩት አውሮፕላን ማረፊያ እንደተነሳ አየር ላይ ተበታትኖ ሜዲቴራንያን ባህር ላይ የወደቀው የኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላን አደጋ መንስኤ በመጣራት ላይ መሆኑን የኢትዮጵያ አየር መንገድ አስታወቀ ።

https://p.dw.com/p/LgUC
የኢትዮጵያ አየር መንገድ 737-800 አውሮፕላንምስል AP

የአየር መንገዱ ስራ አስኪያጅ አቶ ግርማ ዋቄ ዛሬ እንደተናገሩት አስራ አራት አባላት የሚገኙበት የአየር መንገዱ አጣሪ ቡድን ወደ ቤይሩት ሄዷል ። የኢትዮጵያ አየር መንገድ እንደሚለው ትናንት ለሊት የተከሰከሰው ቦይንግ 730-800 አውሮፕላን አየር መንገዱ ኤሮ ስፔስ ከተባለው ድርጅት ተከራይቶ የሚገለገልበት አውሮፕላን ነው ።

Libanon Flugzeugabsturz Rettungsaktion vor der Küste
መርከቦች በፍለጋ ላይምስል AP

አደጋ የደረሰበት የኢትዮጵያዉ አዉሮፕላን ለገጠመዉ ችግር ምክንያት የሆነዉ ምንድ ነዉ የሚለዉ እስካሁን እየተጣራ ያለ ጉዳይ ነዉ። አደጋዉ ከሽብር ጋ ግንኙነት እንደሌለዉ ከልባኖስና ኢትዮጵያ መንግስታት ተነግሯል። አዉሮፕላኑ አየር ሆኖ ለአራት ተከፋፍሎ ባህር ላይ መከስከሱ ነዉ የሚገለጸዉ።ከአፍሪቃ አየር መንገደች አዳዲስ አውሮፕላኖችን በመግዛት እና ወደ ሀምሳ ስድስት አገራት በመብረር በአንጋፋነቱ የሚጠቀሰው የኢትዮጵያ አየር መንገድ በዓለም ከፍተኛ ተወዳዳሪዎች ከሚባሉት አየር መንገዶች ተርታ ይሰለፋል ።

Libanon Flugzeugabsturz Trümmer an der Küste Mittelmeer
ከባህር ውስጥ የተለቀሙ ዕቃዎችምስል AP

በትርፋማነቱ የሚታወቀው ይኽው አየር መንገድ በበራ ዋስትናው ዝና ካተረፉ አየር መንገዶች ጋር ይጠቀሳል ። አየር መንገዱ በእስከዛሬ ታሪኩ የአሁኑን ሳይጨምር እ.ጎ.አ ከ 1980 በኃላ ሁለት አሰቃቂ የአውሮፕላን አደጋዎች ናቸው የደረሱበት ።

ታደሰ ዕንግዳው ከአዲስ አበባ የወጡ መግለጫዎችን ተከታትሏል

ሸዋ ለገሰ ወደቤይሩት ደዉላ ዘገባ አጠናቅራለች።

ጌታቸው ተድላ የአየር መንገዱን የአደጋ ታሪክ ተመልክቷል

ሂሩት መለሰ

ተክሌ የኋላ