1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ሩስያ እና ዩኤስ አሜሪካ

ቅዳሜ፣ መስከረም 8 2008

የዩኤስ አሜሪካ የዉጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጆን ኬሪ በአዉሮጳ የሚታየዉ የስደተኛ ችግር « የሰብዓዊ ቀዉስ» ነዉ ሲሉ ገለፁ። ዩኤስ አሜሪካ 10 ሺህ የሶርያ ስደተኞችን ብቻ መዉሰድ በመፈለግዋ በቂ እንዳልሆነም ተናግረዋል።

https://p.dw.com/p/1GZCy
Großbritannien US-Außenminister John Kerry
ምስል picture-alliance/AP Photo/E. Vucci

እንድያም ሆኖ ስደተኞችን ወደ ሃገራት ማምጣቱ ብቻ የችግሩ መፍትሄ እንዳልሆነና ችግሩን ከመሰረቱ መፍትሄ ማግኘት እንደሚገባ ተናግረዋል። ኬሪ በለንደኑ ጉብኝታቸዉ በሶርያ የርስ በርስ ጦርነት ከሩስያ ጋር « እስላማዊ መንግሥት» እያለ ራሱን የሚጠራዉን ቡድን በመዋጋት የጋራ አቋም እንዳላቸዉ ገልፀዋል። በሌላ በኩል ሩስያ የአሳድን መንግሥት ወታደራዊ ድጋፍ በመስጠትዋ ሁለቱ ሃገራት የነበራቸዉ የጋራ ወታደራዊ ዉይይት መቋረጡ ይታወቃል። በዋሽንግተን የሚገኘዉ የአሜሪካ መከላከያ ሚኒስቴር ዛሬ እንዳስታወቀዉ የአሜሪካዉ መከላከያ ሚኒስትር አሽተን ካርተር እና የሩስያ አቻቸዉ ሰርጌይ ሾይጉ ስልክ ተደዋዉለዋል፤ ሁለቱ ሃገራት ዳግም ወታደራዊ ዉይይትን ጀምረዋል። የዉጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጆን ኬሪ ነገ በርሊን እንደሚገቡ ይጠበቃል።

አዜብ ታደሰ

ልደት አበበ