1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ሰላማዊ ሰልፍ በሀዋሳ 

ሐሙስ፣ የካቲት 14 2011

ከሀዋሳና ከሲዳማ ዞን አጎራባች ወረዳዎች በመነሳት በከተማዋ ስታዲየም የተሰበሰቡት ሰልፈኞች ለክልላዊ መዋቅር ጥያቄው ምላሽ ይሰጣል የተባለው ህዝበ ውሳኔ በአፋጣኝ ገቢራዊ እንዲሆን ጠይቀዋል፡፡

https://p.dw.com/p/3Do2A
Äthiopien, Demonstration in Hawassa
ምስል DW/S. Wegayehu

ዛሬ ሀዋሳ ውስጥ በብዙ ሺህ የሚቆጠሩ ነዋሪዎች የሲዳማ ህዝብ ያቀረበው የክልል መዋቅር ጥያቄ በአፋጣኝ ተግባራዊ ይሁንልን ሲሉ በሰላማዊ ሰልፍ ጠየቁ፡፡ ከሀዋሳና ከሲዳማ ዞን አጎራባች ወረዳዎች በመነሳት በከተማዋ ስታዲየም የተሰበሰቡት ሰልፈኞች ለክልላዊ መዋቅር ጥያቄው ምላሽ ይሰጣል የተባለው ህዝበ ውሳኔ በአፋጣኝ ገቢራዊ እንዲሆን ጠይቀዋል፡፡ ዛሬ ከተካሄደው ሠልፍ ጋር ተያይዞ ሁከትና ግርግር ሊነሳ ይችላል በሚል ሥጋት በከተማዋ የሚገኙ ትምህርት ቤቶች እና የንግድ ተቋማት በከፊል ተዘግተው ውለዋል፡፡ ይሁንእንጂ የሰልፉ መረሃግብር በሰላማዊ መንገድ መጠናቀቁን ነው የተነገረው ፡፡ ሰላማዊ ሰልፉን የተከታተለው የሀዋሳው ወኪላችን ሸዋንግዛው ወጋየሁ ተከታዩን ዘግቧል፡፡

ሸዋንግዛው ወጋየሁ

ኂሩት መለሰ

ሸዋዬ ለገሠ


 

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ