1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ሰላም የራቃት ኢራቅና አስተዳደሯ

ማክሰኞ፣ ታኅሣሥ 12 2003

ሁከትና ጥቃት ባላባራባት ኢራቅ ለሁለተኛ ጊዜ በተካሄደዉ አጠቃላይ የምክር ቤት ምርጫ አመፃዉን ተቋቁመዉ በርካታ ዜጎች ድምጽ መስጠታቸዉ አይዘነጋም።

https://p.dw.com/p/Qi6l
የኢራቅ ርእሰ-ብሔር ጃላል ታላባኒ፤ ባለፈው ኅዳር ፣ጠ/ሚንስትር ኑሪ ኧል ማሊኪ፣ ቀጣዩን መንግሥት ይመሠርቱ ዘንድ ሲጠይቁ፣ምስል AP

የምርጫ ዉጤቱን ተከትሎ ግን ባልተረጋጋችዉ አገር ፖለቲከኞች መካከል አለመግባባት በመፈጠሩ፤ ኢራቅና ኢራቃዉያን የአሸባሪዎችን ጥቃት እያስተናገዱ ካለህጋዊ መንግስት ዘጠኝ ወራትን ለመግፋት ተገደዋል። ዛሬ ግን የአገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ኑሪ አልማሊኪ የአገሪቱን የፖለቲካ ዉጥረት ለመለወጥ እንዲቻል ፖለቲከኞች ከስምምነት መድረሳቸዉን አመልክተዋል። ከጅዳ ፣ ነቢዩ ሲራክ የሚከተለውን ዘገባ ልኳል።

ነቢዩ ሲራክ

ሸዋዬ ለገሠ