ስለቦይንግ የኢትዮጵያዊው ባለሞያ አስተያየት
ማክሰኞ፣ መጋቢት 10 2011ማስታወቂያ
መጋቢት 1 ቀን የኢትዮጵያ ውስጥ ተከስክሶ ለ157 ሰዎች ሞት ምክንያት የኾነው አሜሪካ ሠራሹ ቦይንግ 737 ማክስ 8 አውሮፕላን ችግር ቀድሞውኑም ይታወቅ ነበር ተባለ። በሰሜን አሜሪካ የተቋቋመው የቀድሞው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ሠራተኞች ማኅበር ምክትል ፕሬዚደንት እና የበረራ ባለሞያው አቶ ተስፋዬ መኮንን የአውሮፕላኑን ችግር «ቦይንግ ቀድሞ ዐውቆታል» ብለዋል። የሰሜን አሜሪካ አውሮፕላን አብራሪዎች የአውሮፕላኑን ችግር ዐውቀው ላብራሪዎቻቸው ስልጠና ቀደም ብለው እንደሰጡ ተናግረዋል። የኢትዮጵያ ቦይንግ 737 ማክስ 8 አውሮፕላን እና የኢንዶኔዢያው «Lion Air » አውሮፕላን የአደጋ መንስዔ ተመሳሳይ እንደኾነ ተገልጧል።
መክብብ ሸዋ
ማንተጋፍቶት ስለሺ
አዜብ ታደሰ