1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ስለ አቶ መለስ የጤና ሁኔታ የመንግስት መግለጫ

ዓርብ፣ ሐምሌ 13 2004

በህመም ሳቢያ የዕረፍት ጊዜ እንዲወስዱ ሀኪም እንዳዘዘላቸው የተነገረላቸው የኢትዮጵያ ጠ/ሚንስትር አቶ መለስ ዜናዊ፣ በሌሉበት አገሪቱን የሚያስተዳድራት ማን ነው የሚል ጥያቄ መቅረቡን ፣ የፖለቲካ ተንታኞች በዛሬው ዕለት ገለጡ።

https://p.dw.com/p/15cRJ
meles im sessel.jpg Ethiopian Prime Minister Meles Zenawi is seen at his offices in the capital, Addis Ababa, Wednesday, Jan. 10, 2007. Zenawi said Wednesday that a U.S. airstrike in Somalia had not killed any civilians and, in his opinion, would not help create an Iraq-style insurgency or hinder efforts to build a peacekeeping force in the country. (AP Photo/Les Nauheus)
ምስል AP Photo

በህመም ሳቢያ የዕረፍት ጊዜ እንዲወስዱ ሀኪም እንዳዘዘላቸው የተነገረላቸው የኢትዮጵያጠ/ሚንስትር አቶ መለስ ዜናዊ፣ በሌሉበት አገሪቱን የሚያስተዳድራት ማን ነው የሚል ጥያቄ መቅረቡን ፣ የፖለቲካ ተንታኞች በዛሬው ዕለት ገለጡ።
የአቶ መለስ መንግሥት ፣ የጎሣ ፌደራሊዝምን የፖለቲካ አመራር ዘይቤው ቢያደርግም፤ የማዕከላዊው አስተዳደር ጥብቅ ቁጥጥር፤ በገዥው ፓርቲ እጅ ነው ሲል AFP አስታውቋል። በህገ-መንግሥቱ መሠረት፣ ጠ/ሚንስትሩ በማይኖሩበት ጊዜ ፣ ምክትል ጠ/ሚኒስትሩ ናቸው ወክለው መሥራት የሚጠበቅባቸው።
ስለ ጠቅላይ ሚንስትር መለስ ጤንነት ይዞታ በተናፋሽ ወሬ ብዙ የሚባል ቢኖርም፤ ትናንት የኢትዮጵያ ባለሥልጣናት፤ የ 57 ዓመት ዕድሜ ያላቸው አቶ መለስ፤ ጤንነታቸው ተመልሶአል ወይም ተስተካክሏል ሲሉ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል። የኢትዮጵያ የመገናኛ ዘዴዎች(Communication )ሚንስትር አቶ በረከት ስምዖን---

«የጤንነታቸው ይዞታ በጣም ጥሩና የተመለሰላቸው ሲሆን፣ ከዚህ በተጨማሪ ፣ ጠ/ሚንስትሩ፣ ባለፉት ዐሠርተ-ዓመታት ፣ በመንግሥት ሥራ ጫና ፣ በተለይ በቅርብ ጊዜያት ፣ --እንዲሁም በዓለም አቀፍ መድረኮች ባላቸው ድርሻ ምክንያት፣ --ሀኪሞቻቸው፣ ሥራ አቁመው ዕረፍት ያደርጉ ዘንድ መክረዋቸዋል። ለአናንተ የምነግራችሁ የጤንነታቸው ይዞታ በጠሙን የተመለሰላቸውና በጥሩ ሁኔታ እንደሚገኙ ነው። ከጥቂት ቀናት ፣ የሥራ መቅረት በኋላ፣ ወደ ጽ/ቤታቸው ተመልሰው የመንግሥት ተግባራቸውን ያካሂዳሉ።»
ጌታቸው ተድላ ኃይለ ጊዮርጊስ
ሂሩት መለሰ
ነጋሽ መሃመድ