1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ሶሪያ: የዉጊያ፥ምርጫና ሥጋት ምድር

ረቡዕ፣ ግንቦት 1 2004

መንግሥት የሚቆጣጠረዉ ቴሌቪዥን ጣቢያ በየድምፅ መስጪያ ጣቢያዉ የተሰለፈዉን ሕዝብ ብዛት፥ የድምፅ አሰጣቱን ሒደት፥ ያንቆረቁራል፥የአማፂያን ቪዲዮዎች ደግሞ ፥የቤት-ሕንፃ ፍርስራሽ የተከመረባቸዉ አረዳ-መደብሮች፥ የጎማ፥ እና ተኩስ፥ ዉጊያ ትርምስን ያሳያሉ

https://p.dw.com/p/14sDa
epa03209442 A Syrian woman casts her ballot for parliamentary elections at a polling station in Kafarsouseh area in Damascus, Syria, 07 May 2012. Syrians started voting to choose a new parliament amid a total boycott by the opposition and continued violence that killed at least 11 people. The election initially scheduled for September was postponed due to the uprising against President Bashar al-Assad. A total of 7,195 candidates including 710 women registered to contest the 250 seats, according to state news agency SANA. EPA/NABIL MOUNZER
ምርጫምስል picture-alliance/dpa

09 05 12

የሶሪያ መንግሥት ጦርና በመንግሥት ላይ ያመፁት ታጣቂዎች ተኩስ ለማቆም የገቡትን ቃል ጥሰዉ በየአካባቢዉ የሚያደርጉት ግጭትና ዉጊያ እንደቀጠለ ነዉ።የተባበሩት መንግሥታት ድርጅትና የአረብ ሊግ ልዩ መልክተኛ ኮፊ አናን ያደራደሩት የተኩስ አቁም መጣሱ በሚያነጋግርበት መሐል ሶሪያ ዉስጥ የምክር ቤት አባላት ምርጫ ተደርጓል።ፕሬዝዳት በሽር አል-አሰድ የምርጫዉን አላማና ሒደት ሲያደንቁ፥ ተቃዋሚዎቻቸዉ አጣጥለዉ ነቅፈዉታል፥ ልዩ መልዕክተኛ ኮፊ በበኩላቸዉ ሶሪያ ወደ ሙሉ የርስ በርስ ጦርነት ትገባለች ብለዉ እንደሚሰጉ አስጠንቅቀዋል።ነጋሽ መሐመድ አጭር ዘገባ አጠናቅሯል።

ገሚሱ ይመርጣል-ይመረጣል።ሌላዉ በየቤቱ አድፍጧል።የተቀረዉ ያምፃል፥ ወይም ይዋጋል። መንግሥት የሚቆጣጠረዉ ቴሌቪዥን ጣቢያ የምክር ቤት እንደራሴዎቹን ለመምረጥ በየድምፅ መስጪያ ጣቢያዉ የተሰለፈዉን ሕዝብ ብዛት፥ የድምፅ አሰጣቱን ሒደት፥ የተፎካካሪዎችን መልዕክት ያንቆረቁራል፥-ሰኞ አንድ፥ ዛሬ ሰወስተኛ ቀኑ።

የአማፂያን ቪዲዮዎች ደግሞ ኦና ቤት-ሠፈሮች፥የቤት-ሕንፃ ፍርስራሽ የተከመረባቸዉ አረዳ-መደብሮች፥ የጎማ፥ ቃጠሎ-ጢስ ጠለስ እና ተኩስ፥ ዉጊያ ትርምስን ሲያሳዩ ነዉ ከሰኞ- ዛሬ የደረሱት።ሶሪያና ሶሪያዎች።ፖለቲከኞቻቸዉም እንደዚያዉ።

«አዉራ-መንገድ የማይወጡት፥ ሕግ የማይጥሱት ወይም የማይገድሉት አብዛኞቹ ሶሪያዉን የተሐድሶ ለዉጥ ይፈልጋሉ።»

ፕሬዝዳት በሽር አል-አሰድ።ለሳቸዉ የሰኞዉ ምርጫ የተሐድሶ ለዉጣቸዉ አካል፥ ለሶሪያዊዉ ፖለቲካዊ ጥያቄ መልስ ሰጪ ነዉ።ከዚሕ ቀደም በዘጠና ከመቶ ድምፅ ፀደቀ በተባለዉ ሕገ-መንግሥት መሠረት እስካሁን በሥልጣን ላይ ያለዉ የባዓዝ ፓርቲ በሚቆጣጠረዉ ምክር ቤት ተቋዋሚዎችም ይገባሉ።

በዚሕም መሠረት ሁለት መቶ ሐምሳ መቀመጫ ላለዉ ምክር ቤት አባልነት በሐገር ዉስጥ ያሉ የአንዳድ ተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲ እጩዎች ተወዳድረዋል።የፕሬዝዳት አሳድ መንግሥት መወገድ አለበት የሚሉት ሐይላት ግን ገሚስ ሶሪያ በደም አበላ እየራሰች የምን ምርጫ ባይ ናቸዉ።«የሶሪያ ብሔራዊ ምክር» የተሰኘዉ የተቃዋሚዎች ስብስብ ቃል-አቀባይ ሎይ ሳፊ ደግሞ የምን ምርጫ-ይላሉ።

«አሳፋሪ ነዉ።ማለቴ ገሚስ ሐገሪቱ ጦርነት ላይ እያለች፥ ጦሩ ከተሞችን እያጠፋ እንዴት ምርጫ ሊደረግ ይቻላል።»

ልዩ መልዕክተኛ ኮፊ አናን የሸመገሉት ስምምነት ዘጠኝ ሺሕ ያሕል ሰዉ የገደለ፥ ብዙ ሺዎችን ያቆሰለ፥ ያሰደደዉን ዉጊያ ጦርነት ለማስቆም ያለመ ነበር።ሥምምነቱ ከፀደቀ ወዲሕ ጦርነቱ መቀነሱ አልቀረም።ሥምምነቱ ወር ሊደፍን ዕለታት ሲቀሩት ትናንት ልዩ መልዕክተኛ ኮፊ አናን ለፀጥታዉ ጥበቃ ምክር ቤት እንደነገሩት ግን ሶሪያ ከለየለት የርስ በርስ ጦርነት እንዳትዘፈቅ ያሰጋል።

Members of the Free Syrian Army hold their rifles as they stand in al-Bayada,Homs, February 29, 2012. Syrian troops launched a ground attack in Homs on Wednesday in an apparent attempt to overrun the rebel-held Baba Amro neighborhood that has endured 25 days of siege and fierce bombardment, opposition sources said. REUTERS/Stringer (SYRIA - Tags: POLITICS CIVIL UNREST) Die Freie Syrische Armee (arabisch ‏الجيش السوري الحر‎ al-Dschaisch as-Suri al-Hurr, französisch Armée syrienne libre, Kürzel ASL) ist die größte bewaffnete Oppositionsgruppe in Syrien.[2] Sie ist mit dem Syrischen Nationalrat verbunden.[
ሆምስምስል Reuters
U.N. Secretary-General Kofi Annan addresses delegates Wednesday, Nov. 15, 2006 at the United Nations Climate Change Conference in Nairobi, Kenya. Secretary-General Kofi Annan told the U.N. conference on climate change Wednesday that it's clear it will cost far less to cut greenhouse-gas emissions now "than to deal with the consequences later."(AP Photo/Karel Prinsloo)
አናንምስል AP


«ሐገሪቱ ወደ ሙሉ የርስ በርስ ጦርነት ትገባለች የሚል ተጨባጭ ሥጋት አለ።የዚሕ እንድምታ ደግሞ አስፈሪ ነዉ።ይሕ እንዲሆን ልንፈቅድ አንችልም።ወታደራዊ እንቅስቃሴዉ በሆነ ደረጃ ቀንሷል።ግጭቱን ለማስቆም የተደረገዉ ሥምምነት ግን በተደጋጋሚ እየተጣሰ ነዉ።የግጭቱ መጠንና ስምነቱን የማወኩ ደረጃ ተቀባይነት የለዉም።»
አናን ይሕን ቢሉም የሠላም ሥምምነቱን የሚታዘቡ ሐይላት ወደ ሶሪያ መዝመታቸዉን እንደቀጠሉ ነዉ።ከሰወስት መቶዉ ታዛቢዎች እስከ ዛሬ ሰባዎቹ ደማስቆ ገብተዋል።ተቃዋሚዎች የአሰድ-ሥርዓትን «ለመቀባባት» ያለመ ያሉት ምርጫ ዉጤትና ፋይዳ እስከ ዛሬ አልታወቀም።የሶሪያ ጉዳይ ግን ልክ እንደ ሶሪያዎች ሁሉ ሐያላኑንም በሩቅ-ርቀት እንዳቃረነ ነዉ።

በተባበሩት መንግሥታት የዩናይትድ ስቴትስ አምባሳደር ሱዛን ራይስ፥-«ዩናይትድ ስቴትስ፥ የአሳድ ሥርዓትና አሳድ ራሳቸዉ እንዲወገዱ የሚደረግባቸዉን ግፊት በማጠናከሩ ላይ እንዳተኮረች ነዉ» ብለዋል ትናንት። ሩሲያዊዉ አቻቸዉ ቪታሊ ቹርኪን ግን የሶሪያ እዉነታ ሌላ ነዉ-ባይ ናቸዉ። ችግር ቢኖርም ሶሪያ በተገቢዉ አቅጣጫ እየተጓዘች ነዉ።እንደ ቹርኪን።

ነጋሽ መሐመድ

ሸዋዬ ለገሠ








ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ