1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

በህፃናት እና ወጣቶች ላይ የሚፈፀሙ ጥቃቶች

ዓርብ፣ የካቲት 29 2005

አንድ ልጅ ወይንም አዳጊ ወጣት እየተደበደበ ተሰቃይቶ ሲያድግ በስነ ልቦናው ላይ መጥፎ ትውስታ ጥሎ እንደሚያልፍ ይታመናል። ተፅዕኖውም ለእድሜ ልክ አብሮ እንደሚቆይ ባለሙያዎች ያስረዳሉ።

https://p.dw.com/p/17szd
Das von der Menschenrechtsorganisation amnesty international herausgegebene Bild zeigt den von Narben übersäten Rücken eines früheren Gefangenen im Iran (1983-84), dessen Aussage und Gutachten in einem Bericht "Beweise für Folter im Iran" (August 1984) enthalten sind. In mehr als 70 Staaten der Welt werden Menschen regelmäßig gefoltert. Dabei machen die Folterknechte auch vor der Mißhandlung von Kindern nicht halt, heißt es im neuen Bericht für die UN-Menschenrechtskommission, der am 4.4.1996 in Genf vorgestellt wurde. Besonders weit verbreitet ist danach die Folter im Nahen Osten, etwa im Irak, Iran, Saudi-Arabien, Syrien und der Türkei sowie in China. Die Foltermethoden sind vielfältig. Sie reichen von Schlägen über Elektroschocks, Vergewaltigung von Männern und Frauen bis hin zu Psychoterror.
ምስል picture-alliance/dpa
Symbolbild: Lehrer schlägt (misshandelt) ein Schüler in der Schule *** Quelle: Kudakyar Lizenz: Frei undatiert, eingestellt Juli 2011
በትምህርት ቤትም ልጆች ያለአግባብ ይቀጣሉምስል Kudakyar

አብዛኛውን ጊዜ በህፃናት ወይንም አዳጊ ወጣቶች ላይ የሚፈፀሙ ጥቃቶች በቤተሰብ ወይንም በቅርብ በሚያውቋቸው ሰዎች እንደሆኑ ይታሰባል። በርግጥ የጥቃቱ አይነት ይለያያል። አዘውትሮ መደብደብ፣ የወሲብ ጥቃትና የመሳሰሉት ልጆች ላይ የሚፈፀሙ ስነ ልቦናን የሚጎዱ ጥቃቶች ናቸው። የዛሬው የወጣቶች አለም እንግዳችን የአካል ብቻ ሳይሆን የአዕምሮ ጠባሳዎች እንዳሉት ያጫውተናል። ለዛሬ ስሙን ዮናታን ብለንዋል። ዮናታን አባቱ ለስራ ወደ ኢትዮጵያ እና ኬንያ ድንበር አካባቢ በሄዱበት ወቅት ተወለደ። አባቱ ስራቸውን እንደጨረሱም ዮናታንን ይዘው ወደ አዲስ አበባ ተመለሱ፤ ኋላም ከዮናታን እናት ጋ ሳይሆን ከሌላ ሴት ጋ ትዳር መሰረቱ ።

ይሁንና ዮናታን የአባቱ ትዳር መመስረት ለአዘውትሮ በአባት መደብደብ ብቸኛ ምክንያት እንደሆነ አያምንም። አባቱ በማንኛውም ሰዓት ሃይለኛ እንደነበሩ ነው ያጫወተን። ዮናታን የአባቱን ቤት ለቆ ወደ ጎዳና ሲወጣ «12 አመቴ እና የሰባተኛ ክፍል ተማሪ ነበርኩ» ይላል። ወጣቱ ስለ በፊት ህይወቱ ማውራት አሁን ድረስ ይከብደዋል። ዮናታን ከቤት ወጥቶ ሲኖር አመታት ተቆጠሩ። ዛሬ የሚኖረው ኑሮ ይሻል ይሆን? መልስ ሰጥቶናል። ሙሉ ዝግጅቱን ከድምፅ ዘገባው ያገኙታል።

ልደት አበበ

ሸዋዬ ለገሰ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ