1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

በሰሜን አሜሪካ የአማራ አስቸኳይ ጊዜ ገንዘብ ማሰባሰብ ግብረ ሃይል በወሎ

ረቡዕ፣ መስከረም 12 2014

በሰሜን ኢትዮጵያ በሚካሄደው ጦርነት ምክንያት ለተፈናቀሉ የወሎና ጎንደር አካባቢ ወገኖች የሰብዓዊ ዕርዳታ በማከፋፈል ላይ መሆኑን በሰሜን አሜሪካ የዐማራ አስቸኳይ ጊዜ ገንዘብ ማሰባሰብ ግብረ ሃይል አስታወቀ::

https://p.dw.com/p/40eVW
Äthiopien Sekota | Amhara Region | IDPs
ምስል Alemnew Mekonnen/DW

በሰሜን አሜሪካ የዐማራ አስቸኳይ ጊዜ ገንዘብ ማሰባሰብ ግብረ ሃይል በወሎ ድጋፍ ማድረጉ

በሰሜን ኢትዮጵያ በሚካሄደው ጦርነት ምክንያት ለተፈናቀሉ የወሎና ጎንደር አካባቢ ወገኖች የሰብዓዊ ዕርዳታ በማከፋፈል ላይ መሆኑን በሰሜን አሜሪካ የዐማራ አስቸኳይ ጊዜ ገንዘብ ማሰባሰብ ግብረ ሃይል አስታወቀ::
የግብረ ሃይሉ ተወካዮች ለዶይቸ ቨለ እንደገለፁት ከአሜሪካና ካናዳ የተወከሉ ልዑካን ከዛሬ ጀምሮ የሚካሄደውን የዕርዳታ ሥርጭት ለማገዝ ኢትዮጵያ ይገኛሉ::
ጥምር ቡድኑ በወሎ አካባቢ ለተፈናቀሉ ወገኖች 12 ሚሊዮን ብር የሚያወጣ የመጀመሪያ ዙር ዕርዳታ እንደሚያከፋፍል የተናገሩት ተወካዮቹ በቀጣይም በጎንደር የዕርዳታ ቁሳቁሶችን ለማከፋፈል ማቀዱን ጠቁመዋል::
ታሪኩ ኃይሉ