በሱዳን ፕሬዚደንት ላይ የተላለፈው የእስር ማዘዣና የዐረቡ ዓለም አስተያየት
ሐሙስ፣ የካቲት 26 2001ማስታወቂያ
የፍርድ ቤቱ ውሳኔ በሱዳን መንግስትና በዳርፉር የተጀመረውን የሰላም ድርድር የሚያሰናክል ነው በሚል የተለያዩ ዐረባውያት ሀገሮች መሪዎችና ህዝቦች ተቃውሞአቸውን እያሰሙ ነው። የዐረቡ ሊግ የፍርድ ቤቱ ውሳኔ ሊቀየር የሚችልበትን መንገድ እንደሚፈልግ ትናንት በጠራው አስቸኳይ ስብሰባ በኋላ አስታውቋል። የሱዳን ህዝብ የዳርፉር ዓማጽያንና የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች የደገፉትን የፍርድ ቤቱን የእስር ማዘዣ በመቃወም ትልቅ ሰልፍ አካሂዶዋል። ነቢዩ ሲራክ
AA/TY