1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

በሳዑዲ አረቢያ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ሮሮ

ሐሙስ፣ ግንቦት 6 2007

ሳዑዲ አረቢያ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ፓስፖርታቸውን ለማሳደስ ወይም በሌላ ለመቀየር ረጅም ጊዜ በመውሰዱ መቸገራቸውን ገለጹ። ነዋሪዎቹ እንደሚሉት ሳዑዲ አረቢያ በተለይም ጂዳ የሚገኘዉ የኢትዮጵያ ቆስላ አሮጌ ፓስፖርታቸዉን ሰብስቦ አዲሱን ግን ለረጅም ጊዜ አልሰጣቸዉም።

https://p.dw.com/p/1FPqm
Australische Einreisestempel in einem deutschen Pass
ምስል imago/Paul von Stroheim

በዚሕም ምክንያት የመኖሪያ ፍቃዳቸዉ ጊዜ ማለፉን ወይም ሊያልፍ መቃረቡን ይናገራሉ። እንደሚሉትም ፓስፖርታቸውን እንዲታደስ ወይም እንዲቀየር ሳዑዲ አረቢያ የሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ የጠየቃቸውን ገንዘብ ቢከፍሉም፤ የታደሰዉን ፓስፖርት ለማግኘት ከአምስት ወራት በላይ ጠብቀዋል። እስካሁን አላገኙትም።

እሸቴ በቀለ

ነጋሽ መሐመድ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ