1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

በስዑዲ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ይዞታ

ዓርብ፣ ታኅሣሥ 18 2006

በስዑዲ ዐረቢያ መዲና በሪያድ፤ በተለይም ማንፉህ በተባለው ቀበሌ ከሁለት ወር በፊት እንደሆነው ሁሉ፤ አሠሳ ፤ ከትናንት በስቲያ በጦር ሠራዊቱ ልዩ ኃይል የተጀመረ ሲሆን፤ የኢትዮጵያ ኤምባሲና ቆንስላ ጽ/ቤት ሕጋዊ የመኖሪያና የሥራ ፈቃድ የሌላቸው

https://p.dw.com/p/1Ahgx
ምስል AFP/Getty Images

የኢትዮጵያ ተወላጆች ፤ በሰላም እጃቸውን ለፖሊስ እንዲሰጡ በተደጋጋሚ ማሳሰቢያ ማቅረባቸው ተነግሯል።መጀመሪያ ሥራ ካሠጣቸው ተያዥ ጋር ግንኙነት የሌላቸው እንደ ሕገ ወጥ ሠራተኞች እንደሚታዩ የስዑዲ መንግሥት አስታውቋል ተብሏል። በዚህ ሁኔታ ቁጥራቸው ከ 80 ሺ እስከ 100ሺ የሚገመት ኢትዮጵያውያን ፣ ሕገ-ወጥ ተብለው አገር እንዲለቁ ሊገደዱ ይችላሉ ቢባልም ፣ አብዛኞቹ ፣ ከተያዥዎቻቸው እውቅና ውጭ ሥራ አግኝተው እየሠሩ የሚኖሩ እንዲባረሩ የሚያደርግ እርምጃ ይወሰዳል ብለው እንደማይገምቱ ነው የሚነገረው። ይሁንና ፣ በሚመጡት ቀናት ሊወሰድ የሚችለው እርምጃ እጅግ አሳሳቢ ሊሆን እንደሚችል ግምት አለ። በዚህ ጉዳይ ላይ ነቢዩ ሲራክ ተከታዩን ዘገባ አጠናቅሮ ልኮልናል።

ነቢዩ ሲራክ

ተክሌ የኋላ

ኂሩት መለሰ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ