በቦይንግ ላይ የተመሰረተው ክስ
ሰኞ፣ ሚያዝያ 28 2011ማስታወቂያ
ቦይንግ 737 ማክስ የተባሉት አውሮፕላኖች የአብራሪዎች የማስጠንቀቂያ ሥርዓት እንደማይሰራ ቢያውቅም ለአየር መንገዶች አለመናገሩን አመነ። ኩባንያው በገዛ መሐንዲሶቹ በአብራሪዎች ክፍል የተገጠመው የማስጠንቀቂያ ሥርዓት እንደማይሰራ ያወቀው በኢንዶኔዥያ የላየን አየር መንገድ ንብረት የሆነ ቦይንግ 737 ማክስ አውሮፕላን ተከስክሶ የ157 መንገደኞች ሕይወት ከመቅጠፉ በፊት በጎርጎሮሳዊው 2017 ዓ.ም. ነበር።
ይኸው የአውሮፕላን አይነት በኢትዮጵያ ተከስክሶ ህይወታቸውን ያጡ ዘጠኝ መንገደኞች ቤተሰቦች በቦይንግ ላይ ፈረንሳይ ፍርድ ቤት ክስ መስርተዋል። ሐይማኖት ጥሩነሕ የከሳሾችን ጠበቃ አነጋግራ የሚከተለውን ዘገባ ልካለች።
ሃይማኖት ጥሩነሕ
ነጋሽ መሐመድ