1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

በተለያዩ የዩናይትድ ስቴትስ ከተሞች የቀጠለዉ ተቃዉሞ

ሰኞ፣ ኅዳር 29 2007

የዩኤስ አሜሪካ ፖሊስ ያልታጠቀ ጥቁሮች ላይ ያደረሰዉን ግድያ ተከትሎ በዩኤስ አሜሪካ የተለያዩ ከተሞች የጀመረዉ ተቃዉሞ በሳምንቱ መጨረሻ በበርካታ ከተሞች እጅግ ጎልቶ መታየቱ ተነግሮአል።

https://p.dw.com/p/1E16u
Ferguson Demo gegen Polizeigewalt 17.08.2014
ምስል Reuters

የዩኤስ አሜሪካ የፀጥታ አስከባሪ ፖሊስ ፈርገሰንና ኒዮርክ ከተማ ዉስጥ ያልታጠቁ ጥቁሮችን መግደሉ ይታወቃል። በዩኤስ አሜሪካ ኦባማ ወደ ስልጣን ከመጡ ወዲህ፤ 53 % ነዋሪዎች በጥቁር እና በነጭ አሜሪካዉያን ዘንድ ያለዉ የዘር ጥላቻ ሻክሮአል ሲሉ እንደሚያምኑ፤ 46 % ጥቁር አሜሪካዉያንም ይኸዉ አይነት እምነት እንዳላቸዉ ይገልፃሉ። 36 % የአሜሪካ ነዋሪ ደግሞ በኦባማ አስተዳደር ምንም አይነት ለዉጥ እንዳልታየ ይህ ሁኔታ በፊትም እንደነበር መግለፃቸዉን የወጣዉ ዝርዝር ያመለክታል። በዩናይትድ ስቴትስ የቀጠለዉን ተቃዉሞ በተመለከተ በዋሽንግተን ዲሲ የሚገኘዉን ወኪላችንን ስቱድዮ ስለ ተቃዉሞ ጠይቀነዉ ነበር።


መክብብ ሸዋ
አዜብ ታደሰ
አርያም አብርሃ