1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

በተመድ የሩስያ ቋሚ አምባሳደር ሞቱ

ሰኞ፣ የካቲት 13 2009

በተመ የሩስያዉ ቋሚ አምባሳደር ቪታሊ ቹርኪን ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ። የ 64 ዓመቱ ቹርኪን ከዚህ ዓለም የመለየታቸዉ ድንገተኛ ዜና የተሰማዉ ሰኞ ምሽት ላይ ነዉ። አምባሳደር ቹርኪን ከጎርጎረሳዉያኑ 2006 ዓ,ም ጀምሮ በተመድ የሩስያ ቋሚ አምባሳደር ሆነዉ አገልግለዋል።

https://p.dw.com/p/2XwOw
Russischer UN-Botschafter Witali Iwanowitsch Tschurkin
ምስል picture-alliance/Photoshot

 
ሞስኮ የሚገኘዉ የሩስያዉ የዉጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቹርኪን 65ኛ የልደት በዓላቸዉን ለማክበር አንድ ቀን ሲቀራቸዉ በድንገት ማረፋቸዉን ከማሳወቅ በስተቀር በዝርዝር የገለፀዉ ነገር የለም። ባለፈዉ ጥቅምት ወር የዉስጥ በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የኤርትራ ቋሚ ተጠሪ ሆነው ሲያገለግሉ የቆዩት አምባሳደር ግርማ አስመሮም በድንገት ማረፋቸዉ ይታወሳል፡፡ የ 68 ዓመቱ አምባሳደር ግርማ አስመሮም ለስራ ወደ ኒው ዮርክ ከመምጣታቸዉ በፊት በኢትዮጵያና በአፍሪካ ኅብረት፣ እንዲሁም በዩናይትድ ስቴትስና በካናዳ የኤርትራ አምባሣደር ሆነው መስራታቸዉ ይታወሳል። 
 
አዜብ ታደሰ
አርያም ተክሌ