1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

በኢትዮጵያ የርቀት ትምህርትን መታገዱ

ሐሙስ፣ ነሐሴ 27 2002

የኢትዮጵያ ትምሕርት ሚኒስቴር ከ 2003 ዓም ጀምሮ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ይሰጥ የነበረው የርቀት ትምሕርት ሙሉ በሙሉ እንዲቋረጥ ያወጣው መመሪያ እያነጋገረ ነው ።

https://p.dw.com/p/P2j5
ምስል DW

የትምሕርት ሚኒስቴር መመሪያው ከጊዜ ወደ ጊዜ እየወረደ የመጣውን የትምሕርት ጥራት ደረጃ ለማሻሻልና ከሐገሪቱ የሰለጠነ የሰው ኃይል ፍላጎት ጋር የሚጣጣም ዓለም ዓቀፍ ደረጃን የጠበቀ ሰልጠና ለመስጠት ያለመ መሆኑን ገልጿል ። በአንፃሩ እገዳው ያለ ቅድመ ማስጠንቀቂያ መጣሉን የሚቃወሙት የግል ዩኒቨርስቲዎች ና ኮሌጆች የትምሕርት ደረጃን ለማስጠበቅ ዓለም ዓቀፍ መስፈርትን አውጥቶ መስራት እንጂ መመሪያ ጥራት ማስጠበቅ አይችልም ሲሉ ይከራከራሉ ።

ታደሰ እንግዳው

ሂሩት መለሰ

ሸዋዬ ለገሠ