1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

በኢትዮጵያ ይካሄዳል የተባለው የስልክና የኢንተርኔት ጠለፋ

እሑድ፣ ሚያዝያ 5 2006

ድርጅቱ በመንግሥት ይፈፀማል ካለው ስለላ ሰለባዎች መካከልም ተቃዋሚዎች ጋዜጠኞች እንዲሁም ፀረ መንግሥት እንቅስቃሴ አካሂዳችኋል ተብለው የታሰሩ ሰዎች ይገኙበታል ። መንግሥት ግን ለአንዳንድ የዜና ወኪሎች በሰጠው ምላሽ ዘገባውን አስተባብሏል ።

https://p.dw.com/p/1Bh2r
Symbolbild Internet Password Hacking
ምስል Fotolia/apops

ዓለም ዓቀፉ የሰብዓዊ መብት ተከራካሪ ድርጅት HRW በኢትዮጵያ የስልክና የኢንተርኔት ስለላ ይካሄዳል ሲል በቅርቡ ባወጣው ዘገባ አጋልጧል ። HRW በዚሁ የጥናት ውጤት መንግሥት የሚቆጣጠረውን የቴሌኮምኒኬሽን መስሪያ ቤትና አገልግሎት የግለሰቦችን ሚሥጥር የመጠበቅን ፣ ሃሳብን በነፃ የመግለፅና የመደራጀትን እንዲሁም መረጃ የማግኘት መብትን ለመገደብ እየተጠቀመበት ነው ሲልም አስታውቋል ። ድርጅቱ በመንግሥት ይፈፀማል ካለው ስለላ ሰለባዎች መካከልም ተቃዋሚዎች ጋዜጠኞች እንዲሁም ፀረ መንግሥት እንቅስቃሴ አካሂዳችኋል ተብለው የታሰሩ ሰዎች ይገኙበታል ። መንግሥት ግን ለአንዳንድ የዜና ወኪሎች በሰጠው ምላሽ ዘገባውን አስተባብሏል ።በመጪው እሁድ የሚተላለፈው እንወያይ በኢትዮጵያ ይካሄዳል የተባለውን የስልክና የኢንተርኔት ጠለፋ እንዲሁም በሃገሪቱ የግለሰቦችን ሚስጥር የመጠበቅና መረጃ የማግኘት መብት ይዞታን ይዳስሳል ። በውይይቱ የተካፈሉት ተሳታፊዎች ከሰነዘሩዋቸው ሃሳቦች የሚከተሉት ይገኙበታል ።

ሂሩት መለሰ

ልደት አበበ