1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

በኤርትራ ላይ የተጠናከረው ማዕቀብ

ማክሰኞ፣ ኅዳር 26 2004

የተመድ የፀጥታ ጥበቃ ምክር ቤት በኤርትራ ላይ የጣለውን ማዕቀብ አጠናከረ።

https://p.dw.com/p/S0Mo

ምክር ቤቱ ትናንት ባስተላለፈው የተጠናከረ የማዕቀብ ውሳኔ መሠረት፡ በሶማልያ ለሚንቀሳቀሱ አሸባሪዎች ከለላ ሰጥተዋል ባላቸው በርካታ የኤርትራ ባለሥልጣናት እና ተቋማት ላይ የንብረት እና የጉዞ ዕገዳ ጥሎዋል። ኤርትራ ከአል ቓይዳ ጋ ግንኙነት አለው ለሚባለው አክራሪ የሶማልያ ዓማፅያን ቡድን አል ሸባብ የገንዘብና የትጥቅ ድጋፍ እንደምትሰጥ የተመድ ገልፆዋል። በናይጀሪያ እና በጋቦ አርቃቂነት የቀረበውን ይህንኑ ማዕቀብ አስራ ሶስቱ አባል ሀገሮች ሲደግፉት፡ ሩስያ እና ቻይና ድምፅ ከመስጠት ተቆጥበዋል። ይሁንና፣ ኤርትራ የተመድ የፀጥታ ጥበቃ ምክር ቤት የጣለባትን ተጨማሪ ማዕቀብ ፍትህ የጎደለው ሕገ ወጥ ነው ስትል በጥብቅ በመቃወም ውሳኔውን እንደማትቀበለው ቀደም ሲል በስልክ ያነጋገርኳቸው የኤርትራ ማስታወቂያ ሚንስትር አቶ አሊ አብዱ አስታውቀዋል።

አበበ ፈለቀ

አርያም ተክሌ

ነጋሽ መሀመድ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ