1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

በየመን የኢትዮጵያውያን ስደተኞች ስቃይ

ሐሙስ፣ ጥር 8 2006

በየቀኑ ኢትዮጵያውያን ከ 3 እስከ 4 በሚደርሱ ጀልባዎች የመን እየገቡ ነው ። እነዚሁ የመን የደረሱ ኢትዮጵያውያን ስደተኞች ለእንግልት ና ለልዩ ልዩ ስቃይ መዳረጋቸውን ዘጋቢያችን አስታውቋል ።

https://p.dw.com/p/1AsB0
Kämpfe im Jemen - Flüchtlinge
ምስል picture-alliance/ dpa

ሳውዲ አረቢያ ህገ ወጥ የምትላቸውን ኢትዮጵያውያንን ጨምሮ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ የውጭ ዜጎችን ብታባርርም አሁንም በርካታ ኢትዮጵያውያን በየመን አቋርጠው ወደ ሃብታም የአረብ ሃገራት መጓዛቸው አላቋረጠም ። የሰነ የመን ዘጋቢያችን ግሩም ተክለ ሃይማኖት እንደዘገበው በየቀኑ ኢትዮጵያውያን ከ 3 እስከ 4 በሚደርሱ ጀልባዎች የመን እየገቡ ነው ። እነዚሁ የመን የደረሱ ኢትዮጵያውያን ስደተኞች ለእንግልት ና ለልዩ ልዩ ስቃይ መዳረጋቸውን ዘጋቢያችን አስታውቋል ። ከሳውዲ አረቢያ ተባረው የመን የገቡ በርካታ ኢትዮጵያውያንም የከፋ ችግር ውስጥ እንደወደቁ ለዶቼቬለ ተናግረዋል ። ነጋሽ መሃመድ ግሩምንና ሁለት የመን የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ስደተኞችን በስልክ አነጋግሯል ።

ግሩም ተክለ ሃይማኖት

ነጋሽ መሃመድ