1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

በጄኔራል ሰዓረ መኮንን ላይ ጥቃት መድረሱ ተረጋገጠ

እሑድ፣ ሰኔ 16 2011

ጠቅላይ ምኒስትር ዐቢይ አሕመድ በኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ጄኔራል ሰዓረ መኮንን ላይ ጥቃት መፈጸሙን ከዕኩለ ለሊት በኋላ በብሔራዊ ቴሌቭዥን ቀርበው አረጋገጡ።

https://p.dw.com/p/3KvVM
Ruanda Kigali - Äthiopiens Premierminister Abiy Ahmed bei Rede zum 25. Gedenktag des Völkermord 1994
ምስል Getty Images/AFP/Y. Chiba

ጠቅላይ ምኒስትር ዐቢይ አሕመድ በኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ጄኔራል ሰዓረ መኮንን ላይ ጥቃት መፈጸሙን አረጋገጡ። ጠቅላይ ምኒስትሩ ከዕኩለ ለሊት በኋላ በብሔራዊ ቴሌቭዥን ቀርበው በሰጡት መግለጫ በባሕር ዳር በተፈጸመው የመፈንቅለ መንግሥት ሙከራ ሰዎች መገደላቸውን እና መቁሰላቸውን ገልጸዋል።

ጠቅላይ ምኒስትሩ በጄኔራል ሰዓረ መኮንን ላይ የተፈጸመው ጥቃት ከባሕር ዳሩ የመፈንቅለ መንግሥት ሙከራ ጋር የተያያዘ እንደሆነ ገልጸዋል።  ጠቅላይ ምኒስትሩ «ይህ በአማራ ክልል ያጋጠመውን ችግር እና የመፈቅለ መንግሥት ሙከራ በከፍተኛ የኃላፊነት ስሜት ሆኖ እያስተባበረ እና እየመራ የነበረውን ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም በቅጥረኛ የተገዙ የቅርብ ሰዎች አሁን አመሻሽ ላይ የምንወደውን የምናከብረውን ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም መሰል ጥቃት ተፈፅሞበታል» ብለዋል።

በጠቅላይ ኤታማዦር ሹሙ ላይ ጥቃት ሰንዝረዋል የተባሉ ሰዎች በቁጥጥር ሥር መዋላቸውንም ተናግረዋል።

እሸቴ በቀለ
ተስፋለም ወልደየስ