በጄኔራል ሰዓረ መኮንን ላይ ጥቃት መድረሱ ተረጋገጠ
እሑድ፣ ሰኔ 16 2011ማስታወቂያ
ጠቅላይ ምኒስትር ዐቢይ አሕመድ በኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ጄኔራል ሰዓረ መኮንን ላይ ጥቃት መፈጸሙን አረጋገጡ። ጠቅላይ ምኒስትሩ ከዕኩለ ለሊት በኋላ በብሔራዊ ቴሌቭዥን ቀርበው በሰጡት መግለጫ በባሕር ዳር በተፈጸመው የመፈንቅለ መንግሥት ሙከራ ሰዎች መገደላቸውን እና መቁሰላቸውን ገልጸዋል።
ጠቅላይ ምኒስትሩ በጄኔራል ሰዓረ መኮንን ላይ የተፈጸመው ጥቃት ከባሕር ዳሩ የመፈንቅለ መንግሥት ሙከራ ጋር የተያያዘ እንደሆነ ገልጸዋል። ጠቅላይ ምኒስትሩ «ይህ በአማራ ክልል ያጋጠመውን ችግር እና የመፈቅለ መንግሥት ሙከራ በከፍተኛ የኃላፊነት ስሜት ሆኖ እያስተባበረ እና እየመራ የነበረውን ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም በቅጥረኛ የተገዙ የቅርብ ሰዎች አሁን አመሻሽ ላይ የምንወደውን የምናከብረውን ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም መሰል ጥቃት ተፈፅሞበታል» ብለዋል።
በጠቅላይ ኤታማዦር ሹሙ ላይ ጥቃት ሰንዝረዋል የተባሉ ሰዎች በቁጥጥር ሥር መዋላቸውንም ተናግረዋል።
እሸቴ በቀለ
ተስፋለም ወልደየስ