ከ1500 በላይ አባወራዎች ተፈናቅለዋል
ዓርብ፣ ጥቅምት 13 2013ማስታወቂያ
በደቡብ ክልል ቤንች ሸኮ ዞን ጉራ ፈርዳ ወረዳ ታጣቂዎች ባለፉት ሁለት ቀናት በፈጸሙት ጥቃት 31 ሰዎች ገደሉ።በጥቃቱ ሌሎች አምስት ሰዎችም ቆሰለዋል። ከአንድ ሺህ አምስት መቶ በላይ አባወራዎችም አካባቢያቸውን ለቀው ሸሽተዋል።በአሁኑ ጊዜ ነዋሪዎቹ በወረዳው ሹቢ እና አሮጌ ብረሃን የተባሉ ቀበሌያትን በመልቀቅ ቢፍቱ በተባለች አነስተኛ ከተማ ላይ ተጠልለው እንደሚገኙ ለዶይቸ ቬለ (DW ተናግረዋል ።
ሸዋንግዛው ወጋየሁ
ኂሩት መለሰ
አዜብ ታደሰ