1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

በጉራፈርዳ ወረዳ ነዋሪዎች ተፈናቀሉ

ሰኞ፣ ግንቦት 30 2013

በደቡብ ክልል ቤንች ሸኮ ዞን ጉራፈርዳ ወረዳ ታጣቂዎች ከአራት ሺህ በላይ ነዋሪዎችን አፈናቀሉ። የአካባቢው ነዋሪዎች እንዳሉት መፈናቀሉ የተከሰተው የታጠቁ ቡድኖች ዓርብ ዕለት ስድስት የፀጥታ አባላትን ገድለው ወደ መንደሮቹ ከገቡ በኋላ ነው።

https://p.dw.com/p/3uXsz
Karte Äthiopien englisch

«የፀጥታ ኃይሎችም ተገድለዋል»

በደቡብ ክልል ቤንች ሸኮ ዞን ጉራፈርዳ ወረዳ ታጣቂዎች ከአራት ሺህ በላይ ነዋሪዎችን አፈናቀሉ። የአካባቢው ነዋሪዎች እንዳሉት መፈናቀሉ የተከሰተው የታጠቁ ቡድኖች ዓርብ ዕለት ስድስት የፀጥታ አባላትን ገድለው ወደ መንደሮቹ ከገቡ በኋላ ነው። ታጣቂዎቹ ቅዳሜና እሁድ በወረዳው ጋቢጣና ሰመርታ በተባሉ ቀበሌያት የመኖሪያ ቤቶችን አቃጥለዋል፣  በማሳ ላይ የነበረ ሰብልም አውድመዋል። ዶቼ ቬለ (DW) ያነጋገራቸው በደቡብ ክልል ቤንች ሸኮ ዞን የጉራፈርዳ ወረዳ የፀጥታ ባለሥልጣናት በቁጥር ባይጠቅሱም በወረዳው በፀጥታ አባላት ላይ ጥቃት መድረሱንና የመኖሪያ ቤቶች መቃጠላቸውን አረጋግጠዋል።

 ሸዋንግዛዉ ወጋየሁ 

ሸዋዬ ለገሠ

ማንተጋፍቶት ስለሺ