1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ባንጉዊ በሤሌካ በዓማጺያን ተያዘች

እሑድ፣ መጋቢት 15 2005

የማዕከላዊት አፍሪቃ ሬፑብሊክ ዓማጺያን ዋና ከተማይቱን ባንጉዊን መቆጣጠራቸውን የአገሪቱ መንግሥት አስታወቀ።

https://p.dw.com/p/183Ru
Seleka rebel coalition member, which launched a major offensive last month, hold on January 10, 2013 a position in a village 12 kms from Damara, where troops of the regional African force FOMAC are stationned. Rebels in Central Africa on March 22, 2013 were advancing on the capital Bangui after forcing their way through a key checkpoint manned by international forces, a military source told AFP. The rebels from the Seleka coalition had shot their way through the Damara checkpoint, some 75 kilometres (47 miles) north of the capital, around 1100 GMT, said a source with the Multinational Force of Central Africa (FOMAC) which was manning the roadblock. AFP PHOTO/ SIA KAMBOU (Photo credit should read SIA KAMBOU/AFP/Getty Images)
ምስል AFP/Getty Images

ዓማጺያኑ ከአጭር ውጊያ በኋላ የፕሬዚደንቱን ቤተ-መንግሥት ሲይዙ የአገሪቱ መሪ ፍራንሱዋስ ቢዚዜም ወደ ኮንጎ መሸሻቸው ተያይዞ ተጠቅሷል። ዓማጺያኑ ቦዚዜን ባለፈው ጥር ወር ተደርጎ የነበረ የሰላም ውልን አላከበሩም ሲሉ በመወንጀል ከሥልጣን ለማስወገድ የጥቃት ዘመቻ ሲያካሂዱ መቆየታቸው የሚታወስ ነው። የሰላሙ ውል ተኩስ-አቁምን፣ የሽግግር መንግሥት ምስረታንና በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ ምርጫ መካሄዱን የሚጠቀልል ነበር። ይህ በዚህ እንዳለ ፈረንሣይ የአገሪቱን አሳሳቢ ሁኔታ በማጤን የተባበሩት መንግሥታት ጸጥታ ም/ቤት በጉዳዩ አስቸኳይ ስብሰባ እንዲያካሂድ እንደገና ጥሪ አድርጋለች። ማዕከላዊት አፍሪቃ ሬፑብሊክ ውስጥ በወቅቱ 250 የፈረንሣይ ወታደሮች ሰፍረው የሚገኙ ሲሆን የነዚህም ተግባር የአገሪቱን ዓለምአቀፍ አየር ጣቢያና 1250 ገደማ የሚጠጉ የፈረንሣይ ዜጎችን በመጠበቅ የተወሰነ ነው።

መስፍን መኮንን

ልደት አበበ