1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ብሪታንያ የሶሪያ ስደተኞችን ልትቀበል ነዉ

ሐሙስ፣ መስከረም 6 2008

የብሪታንያ መንግሥት ስደተኞቹን የሚቀበለዉ በሶሪያ አጎራባች ሐገራት ከሠፈሩት ስደተኞች መሐል እንጂ አዉሮጳ የገቡትን አይደለም።ያም ሆኖ ብሪታንያ በአምስት ዓመት ጊዜ ለመቀበል ያቀደችዉ ስደተኛ ቁጥር በሁለት ቀናት ዉስጥ ወደ ጀርምን የገቡትን ቢያክል ነዉ

https://p.dw.com/p/1GY9a
ምስል Reuters/P. Nicholls

[No title]

እንደ አብዛኞቹ የምሥራቅ አዉሮጳ መንግሥታት ስደተኞች እንዳይገቡባት ድንበሯን እስከ መዝጋት የደረሰችዉ ብሪታንያ ሰሞኑን ግትር አቋሟን ለዘብ ያደረገች መስላለች።የብሪታንያ መንግሥት ከሐገሩ ሕዝብ በደረሰበት ጫና ምክንያት በአምስት ዓመት ዉስጥ ሐያ ሺሕ የሶሪያ ስደተኞችን ለማስተናገድ ማቀዱን አስታዉቋል።የብሪታንያ መንግሥት ስደተኞቹን የሚቀበለዉ በሶሪያ አጎራባች ሐገራት ከሠፈሩት ስደተኞች መሐል እንጂ አዉሮጳ የገቡትን አይደለም።ያም ሆኖ ብሪታንያ በአምስት ዓመት ጊዜ ለመቀበል ያቀደችዉ ስደተኛ ቁጥር በሁለት ቀናት ዉስጥ ወደ ጀርምን የገቡትን ቢያክል ነዉ።ሃያ ሺሕ።የለንደኑ ወኪላችን ድልነሳ ጌታነሕ ዝርዝር ዘገባ ልኮልናል።

ድልነሳ ጌታነሕ

ነጋሽ መሐመድ

ሒሩት መለሠ