1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ቮልስቫገን ከኢንቨስትመንት ኮሚሽን ጋር ተፈራረመ

ሰኞ፣ ጥር 20 2011

ቮልስቫገን ከኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ስምምነት ተፈራረመ። ምምነቱ በርካታ የጀርመን ኩባንያዎችን ወደ ኢትዮጵያ ይስባል ተብሎ ይጠበቃል። 

https://p.dw.com/p/3CKkF
Steinmeier Äthiopien VW
ምስል DW/L. Schadomsky

 

Steinmeier Äthiopien VW
ምስል DW/L. Schadomsky

የጀርመኑ የመኪና አምራች ግዙፍ ኩባንያ ቮልስቫገን ከኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ጋር የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረመ። ኩባንያው ይህን የመግባብያ ስምምነት ሲፈራረም በኢትዮጵያ የመኪና መገጣጠሚያ ፋብሪካ ለማቋቋም ያስችላል ተብሎአል። ስምምነቱን የተፈራረሙት የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ አበባ አበባዬሁ እና በደቡብ አፍሪካ የቮልስቫገን ዋና ሥራ አስኪያጅ ቶማስ ሼፈር ናቸዉ።

Steinmeier Äthiopien VW
ምስል DW/L. Schadomsky

የመግባብያ ስምምነቱ ሲፈረም ኢትዮጵያን በመጎብኘት ላይ የሚገኙት የጀርመኑ ፕሬዚዳንት ፍራንክ ቫልተር ሽታይን ማየር እና የኢትዮጵያ የገንዘብ ሚኒስትር አቶ አህመድ ሽዴ ተገኝተዋል። የጀርመኑ ፕሬዚዳንት ፍራንክ ቫልተር ወደኢትዮጵያ ሲጓዙ የጀርመን ባለወረቶችንና የኤኮኖሚ ጉዳይ ባለሞያዎችን ይዘዉ ነዉ። ስምምነቱ በርካታ የጀርመን ኩባንያዎችን ወደ ኢትዮጵያ ይስባል ተብሎ ይጠበቃል። 


አዜብ ታደሰ