1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ተጠናክሮ የቀጠለው የዩክሬይን ውዝግብ

ማክሰኞ፣ ታኅሣሥ 1 2006

ፕሬዚደንት ቪክቶር ያኑኮቪች የሚመሩት የዩክሬይን መንግሥት ከአውሮጳ ህብረት ጋ የፖለቲካ እና የንግድ ትብብር ስምምነት ለመፈረም ዝግጁ ባለመሆኑ በሀገሪቱ ካለፉት ሁለት ሳምንታት ወዲህ ግዙፍ ተቃውሞ እንደቀጠለ ነው።

https://p.dw.com/p/1AWWi
ምስል picture-alliance/AP

ከሀያ ቀናት በፊት በዚያን ጊዜ የአውሮጳ ህብረት ፕሬዚደንት በነበረችው በሊትዌንያ መዲና ቪልኒዩስ በተካሄደው የአውሮጳ ህብረት እና የምሥራቃዊ አውሮጳ ሀገራት የጋራ ጉባዔ ላይ ይፈረማል ተብሎ የተጠበቀውን የዩክሬይን እና የህብረቱን የፖለቲካ እና የንግድ ትብብር ስምምነት ፕሬዚደንት ያኑኮቪች ባለመፈረማቸው ነበር ተቃውሞው የተነሳው። ይኸው ሁኔታ ዩክሬይንን ወደ ከፋ የፖለቲካ ቀውስ ውስጥ እንዳይጥላት በርካታ የዓለም መሪዎች እና ዲፕሎማቶች ስጋታቸውን እየገለጹ ነው።

ገበያው ንጉሤ

አርያም ተክሌ

ነጋሽ መሀመድ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ