1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ታዳሽ ፣ የፀሐይ ኃይል ምንጭ ፕሮጀክት

ረቡዕ፣ መጋቢት 11 2005

ባለፈው ሳምንት ሳይንስና ኅብረተሰብ ቅንብራችን፣በፀሐይ ኃይል የተበከለ ውሃን ፣ የጤና እክል እንዳያስከትል ሆኖ እንዲቀርብ ማድረግ የሚቻልበትን ሁኔታ በማስተዋወቅ ላይ ካለው የኦስትሪያና የእስዊትስዘርላንድ ድርጅት ተጠሪ ጋር ቃለ ምልልስ አድርገን

https://p.dw.com/p/180oh
ምስል picture-alliance/dpa

እንደነበረ ይታወስ ይሆናል። ኢትዮጵያ ውስጥ ፕሮጀክቶች ካሏቸው ድርጅቶች መካከል « ሄሊዮዝ»ና አንዳንድ «የፀሐይ ሱቅ » የሚል ዓይነት ስም የያዙ በፀሐይ ኃይል ኤሌክትሪክ በማመንጨት ፣ ለቤተሰብም ሆነ ማኅበረሰብ አገልግሎት መስጠት እንደሚቻል ፤ በሐኖፈሩ የዘንድሮ ዓለም አቀፍ ትርዒት የፈጠራ ውጤቶቻቸውን ያሳዩ ኩባንያዎች ነበሩ።

Proteste gegen Kürzungen der Solarförderung
ምስል picture-alliance/ZB

ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ፣ እንደሚታወቀው፣ በኢንዱስትሪ የበለጸጉ በቴክኖሎጂውም የደረጁ መንግሥታት ፤ የኃይል ምንጭ ን በተመለከተ ዐቢይ ግምት በመስጠት ላይ ያሉት ታዳሽ የኃይል ምንጭ ለሚባለው መሆኑ የታወቀ ነው። ይህ፣ ለተፈጥሮ አካባቢ ጠንቅ አለመሆኑ የሚነገርለት ፣ በፀሐይ በነፋስ በውሃና በመሳሰለው ላይ ያተኮረው የኃይል ምንጭ ዘርፍ ፤ ገና በማደግ ላይ በሚገኙት አገሮች ቢስፋፋ እጅግ እንደሚበጅ ከቶ አያጠራጥርም።

Solare Heimanlagen Afrika
ምስል FRES

በዚህ በጀርመን ሀገር ፤ አንዳንድ ኢትዮጵያውያን ከጀርመናውያን ጋር በመተባበር፣ በፀሐይ ኃይል የሚሠራ የኃይል ምንጭ ፤ በተለይ ወደ ውስጥ ገባ ላሉ ንዑሳን ከተሞችና መንደሮች ያላቸውን ጠቀሜታ በመገንዘብ እንዲቀርብ በማድረግ ላይ ሲሆኑ ፣ ከእነዚህ መካከል በደቡብ ምዕራብ ጀርመን ካርልስሩኸ አቅራቢያ «ብሩኅሳል» ላይ የሚገኘው ፣ «አልፋ-ቤት ኢትዮጵያ » (ፊደል ኢትዮጵያ ) እንደማለት ነው)

በዚህ ስያሜ የሚጠራው ፣ በደቡብ ኢትዮጵያ ፣ በጉራጌ አውራጃ በያንቤሊ ሰባካ ፕሮጀክቱን ያስተዋወቀው ድርጅት ነው። አስተባባሪው አቶ ሳሙኤል ኤታና ሁዋ ነው። እርሱም፣ ይኸው ድርጅት ስላበረከተው ድርሻ እንዲህ ያብራራል።

ተክሌ የኋላ

ሂሩት መለሰ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ