1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

አላማ በወጣትነት ሲቀጭ

ዓርብ፣ ኅዳር 20 2006

በደረሰባት የመኪና አደጋ ህይወቷ የተቀየረው እና የአልጋ ቁራኛ የሆነችው የሺወርቅ ምህረቴ

https://p.dw.com/p/1AQDf
Members of the public prosecutor's office and rescuers work on the site of a bus accident on September 9, 2013 in the municipality of San Martin Jilotepeque, Chimaltenango Departament, about 65 km west Guatemala City. A bus carrying scores of passengers plunged down a steep cliff in western Guatemala killing at least 43 people and injuring 40 others, firefighters said. AFP PHOTO / Johan ORDONEZ (Photo credit should read JOHAN ORDONEZ/AFP/Getty Images)
ምስል JOHAN ORDONEZ/AFP/Getty Images

አንዳንዶች ጥሩ ገቢ አግኝተው ህይወታቸውን ለመቀየር ወደ ባህር ማዶ ተጉዘው ባዶ እጃቸውን ወደ ሀገራቸው ይመለሳሉ። ሌሎች በህመም ወይም በአደጋ ህልማቸውን ዕውን ከማድረግ ይሰናከላሉ። በዚህ ክስተት እነሱ ብቻ ሳይሆኑ የሚረዱት ቤተሰባቸውም ጭምር ችግር ይገጥመዋል። የዛሬው የወጣቶች ዓለም ዝግጅት « አላማ በወጣትነት ሲቀጭ» ይሰኛል።

እንግዳችን የሺወርቅ ምህርቴ ትባላለች። የአልጋ ቁራኛ ከሆነች አንድ አመት አለፋት። የሺወርቅን ቅስም የሰበረው አደጋ ከመድረሱ በፊት ተወልዳ ካደገችበት ጎንደር ከተማ ወደ አዲስ አበባ ሄዳ ስራ እየሰራች ቤተሰቧን መርዳትም ችላ ነበር። ይሁንና የ 27 ዓመቷ የሺወርቅ የአንድ ቀን ገጠመኟ የህይወት ጉዞዋን ወዳልገመተችው አቅጣጫ ቀየረው። ለበርካታ ወራት ሆስፒታል ተኝታለች። ህክምናዋን መከታተል እንድትችል ስትልም በአዲስ አበባ በተከራየችው ቤት ትኖራለች። እናቷ ከጎንደር ሊያስታምሟት ሄደው አብረዋት ቀርተዋል። አልተሻላትም፤ አይኗን ስትከድን ትዝ የሚላት አደጋው ነው።

ከፍተኛ ስነ ልቦናዊ ጉዳትም ደርሶባታል።

ህይወቷን ስለቀየረው አደጋ አጫውታናለች። ከድምፅ ዘገባው ያገኙታል።

ልደት አበበ

ነጋሽ መሐመድ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ