አርምሞ ወይም ሜዲቴሽን
ዓርብ፣ ታኅሣሥ 5 2005ይህ ስልት በእስያ እንዲሚገኙ አገሮች እንብዛም ኢትዮጵያ ውስጥ የተለመደ አይደለም። ዮፍታሔ «እናቴ ናት ከጥሞና ጋ ያስተዋወቀችን» ይላል። ከዚያን ጊዜ ጀምሮም የተለያዩ የጥሞና ክህሎቶችን ማወቅና መተግበር ጀምሯል። ይህም ዮፍታሔ እንደሚለው አሁን ለሚማረው ትምህርት ትልቅ አስተዋፅዎ አድርጎለታል። ዮፍታሔ በተለያዩ መንገዶች ስልጠና ይወስዳል፣ እውቀትንም ለሌሎች ያካፍላል። ዮፍታሔ በጥሞና ከራሱ ጋ ሲወያይ አስር አመት ሆኗቷል። ምን ያህል ውጤታማ እንደሆነ ነግሮናል። ዮፍታሔን ለየት የሚያደርገው ሌላው ነበር በየቀኑ ለሚያከናውናቸው ነገሮች ዕቅድ ማውጣቱ ነው። ወጣቱ ያለፈው አመት አንድ « ዊዝደም ስቴፕስ» የሚባል የተማሪዎች እንቅስቃሴ አቋቁሟል። አላማውን ባጭሩ አብራርቶልናል።
ወጣቱ እስካሁን ሰልጥኖ እና አሰልጥኖ ያገኛቸው 50 የምስክር ወረቀቶች አሉት። ከነዚህም ውስጥ የቋንቋ፣ የስፖርት እና የውድድር የምስክር ወረቀቶች ይገኙበታል።
በቅርቡ ከ700 የዮንቨርሲቲ ተማሪዎች ጋ በፈጠራ ክህሎት የፁሁፍ ውድድር ተወዳድሮ በማሸነፉ ወደ ታይላንድ ለሽልማት ተጉዞ ነበር። ዮፍታሔ በአሁኑ ሰዓት « ሸጋ ፌስት ፎር ግሬትነስ» የተሰኘ አገር አቀፍ ስልጠና ለማካሄድ እየተዘጋጀ ነው። ይህም ትምህርቱን ሲያጠናቅ ወደፊት ለማድረግ ካሰበው አላማ ጋ የተጣመረ መሆኑን ገልፆልናል።
ስለአርምሞ ወይንም ሜዲቴሽን ስልት ተማሪ -ዮፍታሔ ማንያዘዋል የሰጠንን ሰፊ ማብራሪያ ከዘገባው ያገኙታል።
ልደት አበበ
ሂሩት መለሰ