1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

አስደንጋጩ የጀርመን አዉሮፕላን አደጋ መንስዔ

ዓርብ፣ መጋቢት 18 2007

በደቡብ ፈረንሳይ በሚገኘዉ ተራራማማ አካባቢ ሰሞኑን የተከሰከሰዉ የጀርመን አዉሮፕላን በቴክኒክ ጉድለት ወይም በሌላ ምክንያቶች ሳይሆን ረዳት አብራሪዉ ሆን ብሎ የፈፀመዉ የጥፋት ርምጃ መሆኑ ተሰምቷል።

https://p.dw.com/p/1Eyd3
Germanwings Absturz 4U9525 Angehörige in Le Vernet
ምስል Reuters/E. Gaillard

ይህ የ144 ተሳፋሪዎችና የ6 የበረራ ሠራተኞችን ሕይወት ያጠፋዉን የአደጋ መንስኤ የፈረንሳይና የጀርመን ፖሊሶች እንዲሁም አቃቤ ሕጉም ጭምር ባካሄዱት ምርመራ መሆኑ ተገልጿል። ይህ ምክንያት ሲሰማም በጀርመን ሕዝብ ዘንድ ዳግም ከፍተኛ ድንጋጤና ቁጣን ቀስቅሷል። ሆኖም ግን ድርጊቱ የሽብር ተግባር እንዳልሆነ የጀርመን መንግሥት የሀገር ዉስጥ አስተዳደር ሚኒስቴር በእርግጠኝነት አስታዉቆአል። የ 27 ዓመቱ ረዳት አብራሪ በመንፈስ መረበሽና ጭንቀት በሽታ ተጠምዶ እንደነበር አንዳንዶች ለብዙኃን መገናኛ ገልፀዋል። ዝርዝሩን የበርሊኑ ወኪላችን ይልማ ኃይለሚካኤል ልኮልናል።


ይልማ ኃይለሚካኤል


አዜብ ታደሰ
ሸዋዬ ለገሠ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ