አወዛጋቢው የአስተዳደር ወሰን እና የማንነት ጉዳዮች ኮሚሽን
ሐሙስ፣ ጥር 30 2011ማስታወቂያ
የኢትዮጵያ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የአስተዳደር ወሰን እና የማንነት ጉዳዮች ኮሚሽን 41 አባላትን አፅድቋል። የኮሚሽኑ ማቋቋሚያ አዋጅ በቅርቡ በነጋሪት ጋዜጣ ታትሞ ይፋ ይሆናል። ይሕ ኮሚሽን ግን በትግራይ ክልላዊ መንግሥት ተቃውሞ ገጥሞታል። ኮሚሽኑን ያቋቋመው አዋጅ ሲጸድቅ ሕገ-መንግሥታዊ ጥሰት ተፈፅሟል ሲል የከሰሰው የትግራይ ክልል ምክር ቤት የትግራይ ክልል መንግስት ስራ አስፈፃሚ ምክር ቤት ጉዳዩን በዝርዝር አይቶ የትርጉም ጥያቄ ለፌደሬሽን ምክር ቤት እንዲያቀርብ አሳስቧል። በኢትዮጵያ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ግንኙነት እና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ዋና ሰብሳቢ አቶ ተስፋዬ ዳባ ግን አዋጁ የቀረበበት እና የጸደቀበት መንገድ ከሕገ-መንግሥቱ ጋር የሚቃረን አይደለም ብለዋል።
እንዳልካቸው ፈቃደ
እሸቴ በቀለ
ኂሩት መለሰ