1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

አይ.ሲ.ሲ እና አፍሪቃ 

ዓርብ፣ ጥር 19 2009

የተቋረጠው የደቡብ ሱዳን የሰላም ጥረትም ከዋነኛ የመወያያ አጀንዳዎቹ ውስጥ ተካቷል ። 54ቱ የአፍሪቃ ኅብረት አባል ሃገራት በሚቀጥለው ሳምንት ጉባኤያቸው ለኅብረቱ ኮሚሽን አዲስ ሊቀመንበርም ይመርጣሉ ።

https://p.dw.com/p/2WWKy
Afrikanische Union Gebäude Außenansicht Äthiopien Addis Ababa
ምስል Imago

Beri AA ICC - Africa Ethiopia - MP3-Stereo

28 ተኛው የአፍሪቃ ኅብረት የመሪዎች ጉባኤ የፊታችን ሰኞ እና ማክሰኞ አዲስ አበባ ውስጥ ይካሄዳል ። ጉባኤው በሁለት ቀናት ቆይታው ትኩረት ሰጥቶ ከሚነጋገርባቸው ውስጥ ሞሮኮ እንደገና የህብረቱ አባል ትሁን አትሁን የሚለው አወዛጋቢ ጉዳይ አንዱ ነው ። የተቋረጠው የደቡብ ሱዳን የሰላም ጥረትም ከዋነኛ የመወያያ አጀንዳዎቹ ውስጥ ተካቷል ። 54ቱ የህብረቱ አባል ሀገራት በሚቀጥለው ሳምንት ጉባኤያቸው ለህብረቱ ኮሚሽን አዲስ ሊቀመንበርም ይመርጣሉ ። ከመሪዎቹ ጉባኤዎች አስቀድሞ የሚካሄደው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ስብሰባም እየተገባደደ ነው ። ከዚሁ ስብሰባ ጎን ለጎን ሰሞኑን አፍሪቃን በተመለከቱ ልዩ ልዩ ጉዳዮች ላይ አዲስ አበባ ውስጥ ውይይቶች ተካሂደዋል ። ከመካከላቸው ዓለም ዓቀፉን የጦር ወንጀለኞች መዳኛ ፍርድ ቤት አይ ሲሲን እና አፍሪቃ የተመለከተው ስብሰባ ይገኝበታል ። የአዲስ አበባው ዘጋቢያችን ጌታቸው ተድላ ኃይለ ጊዮርጊስ ዘገባ አለው  ። 
ጌታቸው ተድላ ኃይለ ጊዮርጊስ 
ኂሩት መለሰ 
አዜብ ታደሰ