1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

አዲሱ የሶማሊያ ጠቅላይ ሚኒስትርና በውጭ የሚኖሩ ሶማሊያውያን አስተያየት

ማክሰኞ፣ የካቲት 10 2001

ባለፈው ሳምንት የተሾሙት አዲሱ የሶማሊያ ጠቅላይ ሚኒስትር ኦማር አብዲራሽድ አሊ ሻርማርኬ የሶማሊያን ውስብስብ ችግሮችን ሊፈቱ እንደሚችሉ ተስፋ ተጥሎባቸዋል ።

https://p.dw.com/p/GwB6
Karte Somalia Spanisch mit Océano Índico, Etiopía, Somalia, Mogadiscio, Kenyaምስል AP Graphics/DW

ጠቅላይ ሚኒስትር ኦማር ሻርማርኬ ሰሞኑን ይፋ እንዳደረጉት ብጥብጥና ሁከትን ከሶማሊያ ለማስወገድ ከአክራሪዎች ጋር መወያየት ይፈልጋሉ ። የአርባ ስምንት ዓመቱ ጎልማሳ ኦማር ሻርማርኬ የትምህርት ደረጃ እና ልምዳቸው እንዲሁም ከሀገሪቱ ውጭ መቆየታቸው ለተሾሙበት ሀላፊነት ብቁ እንደሚያደርጋቸው አሜሪካን የሚኖሩ ሶማሊያውያን ለዶይቼቬለ ተናግረዋል ። ዝርዝሩን አበበ ፈለቀ ያቀርብልናል ።