1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

አዲስ አበባ ለኢትዮጵያውያን ንቅናቄ

ሰኞ፣ መጋቢት 9 2011

የፖለቲካ ፍላጎት እንደሌለው የሚናገረው ንቅናቄው አዲስ አበባ የመላው ኢትዮጵያዊያን እና የአፍሪካ መዲና መሆኗን ስለምናም ለሁለንተናዊ እድገቷ እና ለህዝቦቿ ጥቅም እንጮሃለን ብሏል፡፡ አዲስ አበባ የኢትዮጵያዊነት ማሰሪያ ውል ነች የሚለው ንቅናቄው በመላው ዓለም የሃሳቡ ተጋሪ ከሆኑት ጋር በጉዳዩ ላይ ጠንክሮ እንደሚሰራ አስታውቋል።

https://p.dw.com/p/3FGWj
Äthiopien Addis Abeba
ምስል DW/S. Muchie

 

«አዲስ አበባን እና ሰማይን የኔ ነው» የሚልን አንቀበልም ሲል አዲስ አበባ ለኢትዮጵያዊያን ንቅናቄ ለ«DW» ተናገረ፡፡ ምንም አይነት የፖለቲካ ፍላጎት እንደሌለው የሚናገረው በቅርቡ የተቋቋመው ይኽው ንቅናቄ አዲስ አበባ የመላው ኢትዮጵያዊያን እና የአፍሪቃ መዲና መሆኗን ስለምናምን ለሁለንተናዊ እድገቷ እና ለህዝቦቿ ጥቅም እንጮሃለን ብሏል፡፡ አዲስ አበባ የኢትዮጵያዊነት ማሰሪያ ውል ነች የሚለው ንቅናቄው በመላው ዓለም የሃሳቡ ተጋሪ ከሆኑት ጋር በጉዳዩ ላይ ጠንክሮ እንደሚሰራ አስታውቋል። ሰሎሞን ሙጬ ከአዲስ አበባ ዝርዝሩን ልኮልናል ።
ሰሎሞን ሙጬ
ኂሩት መለሰ
አዜብ ታደሰ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ