1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

አፍሪቃውያን ስደተኞች በእስራኤል

ሰኞ፣ ግንቦት 13 2004

የአፍሪቃውያን ስደተኞች ጉዳይ ተመልካች ድርጅት ስራ አስኪያጅ፤ አቶ ዮሀንስ ባዩ እንዳሉት እስራኤል ውስጥ በአፍሪቃውያን ስደተኞች ላይ የሚደርሰው የጥላቻ ጥቃት ተጠናክሯል።

https://p.dw.com/p/14zQa
epa03124966 African refugees wait for a job offer near the central bus station in southern Tel Aviv, Israel, 27 February 2012. Some 50,000 Africans have entered Israel in recent years, fleeing conflict and poverty in search of safety and opportunity in the relatively prosperous Jewish state. A growing number of African migrants say they were captured, held hostage and tortured by Egyptian smugglers hired to sneak them into Israel. EPA/ABIR SULTAN
ምስል picture-alliance/dpa

ወደ እስራኤል የሚጎርፉት አፍሪቃውያን ቁጥር በብዛት መቀጠሉን የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንጃሚን ኔትናያሁ ትናንት አስታወቁ። «ይህንን መጉረፍ ካላቆምን ቁጥሩ ባንዴ ከ60 ሺ ወደ 600 ሺ ከፍ ይላል» ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ።
ወደ እስራኤል በርካታ አፍሪቃውያን እየተሰደዱ እንደሆነ ይነገራል በብዛትም በግብፅ በኩል አድርገው በርካታ ኤርትራዊያን እና ሱዳናዊያን ይሰደዳሉ። ባለፉት ሳምንታት አንድ እስራኤላዊ ደቡባዊ ቴላቪቭ አፍሪቃውያን ስደተኞች በሚኖሩበት ህንፃ ላይ ጠርሙስ ውስጥ የተሞላ ቤንዚን በእሳት አያይዞ ጥቃት ማድረሱ የሚታወስ ነው። ተጠርጣሪዎቹ በቁጥጥር ስር ውለዋል።
አፍሪቃውያን ስደተኞች ላይ በብዛት በደቡናዊ ቴላቪቭ የሚደርሰው ጥቃት በአፍሪቃውያን ላይ ጥላቻ ስላለ ነው ይላሉ  የአፍሪቃውያን ስደተኞች ጉዳይ ተመልካችን ድርጅት  ስራ አስኪያጅ፤ አቶ  ዮሐንስ ባዩ። አቶ ዮሐንስ የአፍሪቃውያን ስደተኞች ጉዳይን የሚመለከት በእንግሊዘኛው ምህፃር ኤ አር ዲሲ በመባል የሚታወቅ የአፍሪቃውያን ስደተኞች ጉዳይ ተመልካችን ድርጅት ማዕከል ዋና ስራ አስኪያጅ ናቸው። አፍሪቃውያን ስደተኞች ላይ ስለሚደርሰው ጥቃት እና ጊዜያዊ ሁኔታ ከአቶ ዮሐንስ  ጋ የተደረገውን ሙሉ ቃለ ምምልስ ያድምጡ።

ልደት አበበ

epa03124964 African refugees wait for a job offer near the central bus station in southern Tel Aviv, Israel, 27 February 2012. Some 50,000 Africans have entered Israel in recent years, fleeing conflict and poverty in search of safety and opportunity in the relatively prosperous Jewish state. A growing number of African migrants say they were captured, held hostage and tortured by Egyptian smugglers hired to sneak them into Israel. EPA/ABIR SULTAN
ምስል picture-alliance/dpa

ተክሌ የኋላ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ